ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
59

የሻሁራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ማለትም ሎት 1 የደንብ ልብስ ሎት 2 አላቂ የቢሮ እቃዎች፣ ሎት 3 አላቂ የጽዳት እቃዎች እና ሎት 4 የኤሌትሮኒክስ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. በዘርፍ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥ መጠኑ ከብር 100,000 /ከአንድ መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆነ የተጫማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር በወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡ የሰነድ መግዣ ዋጋ ብር 200 /ሁለት  መቶ ብር/ ብቻ ነው፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነድ ኦርጅናልና ኮፒውን በሁለት በታሸገ ኢንቨሎፕ ፖስታ በጥንቃቄ ተሞልቶ በሻ/መ/ደ/ሆስፒታል በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ከህዳር 29/2018 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም በ11፡00 የጨረታ ሳጥኑ ይታሸግና ታህሳስ 14/2018 ዓ.ም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውን በተገኙበት በሻ/የመ/ደ/ሆስፒታል 3:00 ላይ ይከፈታል፡፡
  6. የጨረታ አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ዕቃውን በራሱ ትራንስፖርት ማምጣትና በጥራት ኮሚቴ አስገምግሞ ንብረት ክፍል ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
  7. ሆስፒታሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. በዚህ ጨረታ ማስታወቂያ ያልተካተቱ ህጎችና ደንቦች በግዥ መመሪያው ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡

ማሳሰቢያ፡- አሸናፊ የሚለየው በድምር ነው፡፡

የሻሁራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here