የደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት የመሬት ልማት ማኔጅመንት እና ባንክ ቡድን የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገዉ አዋጅ 721/2004 አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 በፊደል ተራ ከ ሀ እስከ ሠ በተዘረዘረዉ መሰረት የቦታ ስፋታቸዉ እያንዳንዳቸዉ 500 ካ.ሜ 03 (ሶስት) ለድርጅት (ለንግድ) የሚውሉ ቦታዎች በግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች በጨረታ አወዳድሮ ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡
- መጫረት የሚፈልጉ ማንኛዉም ሰዉ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከታህሳስ 06/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የቦታዉን ዝርዝር መረጃ እና ለእያዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል በደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በሥራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ከታህሳስ 06/2018 ዓ/ም እስከ ታህሳስ 17/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ብቻ ይሆናል፡፡
- ቦታዉን መጎብኘት ለሚፈልጉ ተጫራቾች በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚገለጸዉ መርሀ ግብር መሰረት የምናስጎበኝ ይሆናል፡፡
- ጨረታዉ የሚዘጋዉ ታህሳስ 17/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ይሆናል፡፡
- ጨረታዉ የሚከፈተዉ ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 በደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይሆናል፡፡
- ስለጨረታዉ ዝርዝር መረጃ በጋዜጣ እና በአብክመ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ዌብ ሳይት ማየት እንዲሁም በደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ቢሮ በሥራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በሳይት ፕላን ላይ በተገለፀዉ እና በከተማዉ መዋቅራዊ ፕላን መሰረት ደረጃዉን የጠበቀ ግንባታ መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 12 47 58 18 /09 31 63 37 72 በመደወል መረጃ ማግኙት ይችላሉ፡፡
የደጋን ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት

