በሰሜን ጎንዳር ዞን የዳባት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለዳባት ወረዳ ለሁሉም መኪናዎች ዓመታዊ የመኪና መለዋወጫ ዕቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የሚሟላሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑ ግብር የከፈሉ እና የ2018 ዓ.ም የዘመኑን የንግድ ፈቃዳቸውን ያደሱ የ2017 ዓ.ም የታደሰዉ እስከ ታህሳስ 30/2018 የሚያገለግል መሆኑን የሚገልጽ መሆን አለበት፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ፤
- በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- ጨረታው ሲሞላ ሥርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-6 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ዋና እና ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የሚገዙበት ዋጋ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ብቻ ዳ/ወ/ግ/ፍ/ን/አስ/ድጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር ወይም የመለዋወጫ ዋጋ 3 በመቶ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን ዋና እና ኮፒውን በተለያየ ፖስታ አጠቃሎ በማሸግ ዳ/ወ/ግ/ፋ/ን/አስ/ድጋፍ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በተከታታይ 15 ቀናት ከታህሳስ 20/2018 እስከ ጥር 4/2018 ዓ/ም ድረስ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ዳ/ወ/ግ/ፋ/ን/አስ/ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 በቀን ጥር 05/2018 ዓ/ም በ4፡00 ታሽጎ በ4፡30 ይከፈታል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ዳ/ወ/ግ/ፋ/ን/እስ/ ድጋፍ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 113 02 05 ወይም 058 113 04 10 በመደወል መረጃ ማግኙት ይችላሉ፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የጨረታው መክፈቻ ቀን ብሔራዊ በዓል ቀን እንዲሁም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀናት ይከፈታል፡፡
የመኪና ስፔሩ (ድርጅቱ) የምናስጠግንበት ማዕከላዊ ጎንዳር ከተማ ማዕከል መሆን አለበት፡፡
የዳባት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

