በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የኪንፋዝ በገላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 ዓ/ም በመደበኛ በጀት ማስፈፀሚያ የውሃ እቃዎች በግልጽ ጨረታ የግዥ ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ ዉል በመያዝ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡-
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋያነት መለያ ሰርተፊኬት ያላቸው፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ (ሲፒኦ) የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ክፍያ ማዘዣ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከመስሪያ ቤቱ ደረሰኝ በመቁረጥ ማስያዝ የሚችሉ፡፡
- ከዚህ በላይ የተቀመጡትን የመወዳድሪያ መስፈርቶች ማሞላት የምትችሉ ተጫራቾች ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ክፍት ሲሆን በኪን/በገ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ፋይናንስ ቡድን ከረዳት ገንዘብ ያዥ ቢሮ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል መዉሰድ የሚቻል ሲሆን ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸዉን መ/ቤቱ ባዘጋጀዉ የጨረታ ማስገቢያ ሳጥን ዉስጥ ፋይናንሻል ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ ብሎ በመለየት በአንድ በታሸገ ኢንቨሎፕ ፖስታ ዘወትር በስራ ስዓት ከጠዋቱ ከ2፡30-6፡30 እንዲሁም ከስዓት ከ7፡30-11፡30 ድረስ ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የመጫረቻ ሰነዳችሁን ማስገባት ይችላሉ፡፡
- አሸናፊ የሚለየዉ በጥቅል ዋጋ ይሆናል፡፡
- አሸናፊ የሚሆነዉ ድርጅት የዉል ማስከበሪያ (ሲፒኦ) የአሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ክፍያ ማዘዣ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከመ/ቤቱ ደረሰኝ በመቁረጥ ማስያዝ ይችላሉ፡፡
- አሸናፊ የሚሆነዉ ድርጅት ዉል የሚወስደዉ በኪን/በገ/ወ/ፍ/ጽ/ቤት ይሆናል፡፡
- የእቃ እርክክብ ቦታ በኪንፍዝ በገላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ይሆናል፡፡
- ጨረታዉ በአስራ ስድስተኛዉ ቀን 4፡00 ታሽጎ በዚያው ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኘበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ባይገኙም ጨረታዉ የሚከፈት ይሆናል፡፡
- የጨረታ ሰነዱ በተዘጋጀዉ ዝርዝር መግለጫ መሰረት መሞላት ያለበት ሲሆን ከነጠላ ዋጋዉም ሆነ ከጠቅላላ ዋጋዉ ሥርዝ ድልዝ መሆን የለበትም፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- ከጨረታ ሰነዱ ላይ የሚመታዉ ማህተም ከንግድ ሥራ ፈቃዱ ጋር በቀጥታ ተዛማጅ መሆን ይኖርበታል፡፡
- ስለ ጨረታዉ ዝርዝር ማብራሪያ ከፈለጉ በኪን/በገ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 10 በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 09 00 41 59 24 በመደወል መረጃ ማግኙት ይችላሉ፡፡
የኪንፋዝ በገላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

