የቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለቻግኒ ከተማ አስተዳደር ከሚያሰራቸው መሰረተ ልማት ግንባታዎች መካከል አንዱ 04 ቀበሌ የቦሌ ደበታ ድልድይ አፕሮች የጠጠር መንገድ ስራ ሲሆን የዚህን ግንባታ ሎት 2 ቀበሌ 04 ከ ሸህ ያሲን ሙሃመድ ቤት እስከ ወ/ሮ ሞሚና ኡመር ቤት ድረስ ዲዛይን እና ጨረታ ዶክመንት ዝግጅት ስራ በደረጃ 3 እና ከዚያ በላይ የሆኑ አማካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች አንድ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚሰራውን ሥራ ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 150 (አንድ መቶ አምሳ ብር) ብቻ በመክፈል ከቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ በመግዛት መጫረት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ሎት 2 ብር 5,000 (አምስት ሽህ ብር) ብቻ፣ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ)፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ በመሂ 1 ገቢ በማድረግ የደረሰኙን ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፣ ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16 ተኛው ቀን ከረፋዱ 4፡15 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ ጨረታው በወጣ በ16 ተኛው ቀን ከረፋዱ 4፡15 ታሽጎ 4፡30 ይከፈታል፡፡
- የገዙትን የጨረታ ሰነድ በእያንዳንዱ ገጽ በመፈረም የድርጅቱን ማህተም እና አድራሻ አድርጎ መመለስ አለበት፡፡
- የአብክመ ግዥ መመሪያ ቁጥር 1/2003 በተጨማሪ የተሻሻሉ እና የተጨመሩ መመሪያዎች ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡
- ተጫራቾች ለግዥ መመሪያ ተገዥ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- አሸናፊ የምንለየው በሎት በተሞላው ጥቅል ድምር ዋጋ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፣ ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 225 17 21 /058 225 16 31 በመደወል መጠየቅ ትችላላችሁ፡፡
ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት

