በማዕራብ ጎንደር ዞን የምዕራብ በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓ/ም በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 የምዕ/በ/ወ/ሲ/ሰ/የሰ/ኃ/ጽ/ቤት G+1 የቢሮ ግንባታ እንዲሁም ሎት 2 የምዕ/በ/ወ/መንገድ/ት/ጽ/ቤት የደባሪ ወንዝ ድልድይ ግንባታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡- በጨረታው ለመወዳደር መስፈርቱን የሚያሟሉ ተጫራቾች እንድትወዳደሩ እየጋበዝን
- ህጋዊ የሆነ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ ቲን ነበር መለያ ቁጥር ያላቸው፡፡
- ጨረታው የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- ደረጃ Gc 5.bc 4 እና ከዚያ በላይ የሆነ ደረጃ 5 ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ እና ደረጃ 4 ህንፃ ስራ ተቋራጭ እና ከዚያ በላይ የሆኑ፡፡
- ጨረታው የፋይናሻልና ቴካኒካል ሰነድን ይጨምራል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ የጨረታ ሰነዱን ማዕ/ጎንደር/ዞን/ ምዕ/በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ዘወትር በስራ ቀን ቢሮ ቁጥር 13 በመምጣትና ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ፖስታ ማለትም ኦርጅናልና ኮፒ በማለት በጉልህ በተፃፈ አድራሻ ምዕ/በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖረባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚሞሉት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ምዕ/በለሳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 13 ከረዳት ገንዘብ ያዥ ገንዘቡን ገቢ ለማድረግ የገቢ ደረሰኙን ከሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- አሸናፊው አካል ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ የውል ማስከበሪያ በተራ ቁጥር 6 በተገለፀው ተቋም ማስያዝ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት የተጠበቀ ነው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ዋጋ ሲሞላ ሥርዝ ድልዝ ካለው ከፊት ለፊቱ ልዩ ፊርማውን ማስቀመጥ ይኖርበታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ፖስታው ላይም ሆነ ከጨረታ ሰነዱ ስም፣ ፊርማ፣ ማህተም፣ ስልክ ቁጥር እና ሙሉ አድራሻውን መፃፍ ይኖርባቸዋል፡፡
- ይህ ጨረታ በክልሉ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር መመሪያ የሚተዳደር ይሆናል፡፡
- ጨረታው ለተከታታይ 30 ቀናት በጋዜጣ ወጥቶ ይቆያል፡፡
የምዕራብ በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

