ለወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውሉ የሞተር ዘይቶችና ቅባቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቺች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- ንግድ ፈቃድና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎች ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መታሸግ አለበት፡፡ ተጫራቾች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ (የቫት) ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናል ፖስታ በማሸግ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ከጨረታ ሰነዱና ከታሸገው ፖስታ ላይ የድርጅት ማህተም ተነባቢ በሆነ መልኩ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች ያሸነፉበት የስራ (የእቃ) ዋጋ ድምር 10,000 (አስር ሺህ ብር) በላይ ከሆነ 2 በመቶ ተቀንሶ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡ መ/ቤቱ ቫት በመመሪያው መሰረት ይሰበስባል፡፡
- ተጫራቾች የሞሉትን የዋጋ አንድ በመቶ በጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወይም ከተፈቀደላቸው ባንክ በተመሰከረለት (ሲፒኦ) በማስያዝ ከፖስታው ውስጥ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን በወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግዥ ኦፊሰር ቢሮ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታውን ማሸነፋቸው ከተነገራቸው በኋላ ማሻሻያ ማድረግ እና ከጨረታ እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ዝርዝር ማብራሪያ ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የአማራ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ያወጣውን ግዥ አፈጻጸም መመሪያ አዋጅ ቁጥር 1/2003 እና ተሻሽለው ለዉጡ መመሪያዎችና አዋጆች ተገዥ መሆን ይገባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከየካቲት 16/2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 6/2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ተከታታይ ለ21 ቀናት በወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግዥ ኦፊሰር ቢሮ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን እስከ 3፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ መጋቢት 6/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ የጨረታ ሳጥኑ በዚህ ዕለት ከጠዋቱ 3፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመመሪያው መሰረት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታ በሚከፈትበት ወቅት ባይገኙም በመመሪያው መሰረት ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱም የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የጨረታ መክፍቻ ቀን በዓል ቀን ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ቀን ይተላለፋል፡፡
- አሸናፊው ማሸነፉ ተነግሮት ውል ከወሰደ በኋላ ሆስፒታሉ በሚያዘው መሰረት ገዝቶ ማቅረብ አለበት፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ውለታ ከወሰደበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/1008 ዓ/ም ድረሰ ሲታዘዝ ማቅረብ አለበት፡፡
- የተጠቀሰውን ግብዓት በጨረታ አሽናፊው ወጭውን ችሎ የሚቀርብ ይሆናል፡፡
- ውድድሩ በሎት ድምር ነው፡፡
- ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስራ ሂደቱ ስልክ 033 331 01 72 እና 033 331 02 52 ደወሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

