በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን የቻግኒ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ/ም በጀት ዓመት ለሆስፒታሉ አገልግሎት የሚዉሉ ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2 የጽዳት እቃ፣ ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 4 ደንብ ልብስ፣ ሎት 5 ህትመት፣ ሎት 6 የዉሃ እቃ፣ ሎት 7 ኤሌክትሪክ እቃ፣ ሎት 8 የመኪና ጎማ እንዲሁም ሎት 9 ፈርኒቸር ግዥ ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ መስፈርቱን የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳድር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለቸው፡፡
- የግብር ከፈይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸዉ፡፡
- የግዥው መጠን ከብር 200.000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የዕቃዎች (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከተቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቸቻው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የዕቃዎች ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ሰነዱን ቻግኒ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የእለት ገቢ ስብሳቢ ቢሮ ቁጥር 5 የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል መጫረት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ መስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ድረስ ሰነዱን በመሙላት ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር በአንድ ኦርጅናል ፖስታ በማሽግ ተከታታይ ቀናት እስከ 11፡30 ለግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 47 ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ቻ/መ/ደ/ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 47 በ16 ኛው ቀን 3፡00 ታሽጎ በዚያው ቀን 3፡30 ይከፈታል፡፡ ነገር ግን በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሰይ ሰዓት ተሸጎ በተመሳሰይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የገዙትን የጨረታ ሰነድ በእያንዳንዱ ገፅ በመፈረም የድርጅቱን ማህተም አድርጎ መመለስ አለበት፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ያሸነፉበትን ዕቃዎች በተሰጠዉ የግዜ ገደብ ጨርሶ የማሰረከብ ግዴታ አለበቸው፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቁ ነው፡፡
- ውድድሩ በሎት (ጥቅል) ድምር መሆኑን አውቀው የተጠየቁትን የስራ ዝርዝር ሙሉ በሙሉ እንዲሞሉልን እንጠይቃለን፡፡
- እቃዎች ቻ/መ/ደ/ሆስፒታል ድረስ ንብረት ክፍል በማምጣት ገቢ ማድረግ አለበት፡፡
- ሰለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ስልክ ቁጥር 058 556 20 09 ወይም ቻ/መ/ደ/ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 47 ድረስ በአካል በመገኘት መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ቻግኒ የመጀመሪያ ደረጀ ሆስፒታል

