ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
61

የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ2018 በጀት አመት አመታዊ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ውል በመያዝ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  4. የአገልግሎት መጠን ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው በታሸገ በፖስታ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ነገር ግን ከላይ 1-4 የተጠቀሱትን ያላቀረበ ተጫራች ከጨረታው ውጭ ይሆናል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 50 (ሃምሳ ብር) በመክፈል የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍ/ፍ/ቤት የዕለት ገንዘብ ተቀባይ ቢሮ ቁጥር 3 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በመሙላት በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ቢሮ ቁጥር 8 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ከመክፈቻ ቀንና ሰዓት በፊት ማስገባት ይችላሉ፡፡
  8. በሌሎች ተጫራቾች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበራያ (ቢድ ቦንድ) ከሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  10. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኢንቨሎኘ በማድረግ ከየካቲት 16/2018 ዓ.ም እስከ የካቲት 30/2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ 15 ቀን የሚውል ሲሆን በ16ኛው ቀን መጋቢት 01/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡30 ታሽጐ በዚሁ እለት ከረፋዱ 4፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 8 ይከፈታል፡፡ ይህ ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በዚሁ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ቢፈልጉ ቢሮ ቁጥር 8 ድረስ በግንባር ቀርበው ወይም በስልክ ቁጥር 058 775 10 43 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ

የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍ/ፍ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here