በአፈ/ከሳሽ እነ ዋሲሁን ጌታቸው እና በአፈ/ተከሳሽ እነ የኔነህ አለሙ መካከል ባለዉ የገንዘብ ክርክር ጉዳይ እንጅባራ ከተማ 04 ቀበሌ በአዋሳኝ በምሥራቅ መንገድ፣ በምዕራብ ዋና ሳጅን እስከዚያ አሸነፍ፣ በሰሜን ዋ/ሳ ስንታየሁ የኔት እንዲሁም በደቡብ ዋ/ሳ/ ይሁኔ አለሙ መካከል በዋ/ሳጅን አለኽኝ አየነው ስም ተመዝግቦ የሚገኝ የመኖሪያ ቤት በመነሻ ዋጋ ብር 600,000 (ስድስት መቶ ሺህ ብር) ስለሚሸጥ የጨረታ ማስታወቂያን ለ30 ተከታታይ ማለትም ከየካቲት 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መጋቢት 23/2018 ዓ.ም ድረስ ቆይቶ መጋቢት 23/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2፡30 እስከ 6፡30 እንዲሸጥ ሲል ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች ወደ ጨረታው ስትመጡ የጨረታውን መነሻ ዋጋ 1/4 ሲፒኦ ይዛችሁ እንድትቀርቡ ፍርድቤቱ አዝዟል፡፡
የባንጃ ወረዳ ፍርድ ቤት

