ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
16

የጨረታ ቁጥር፡ ጢእ/አካ/01/2026

ኩባንያችን ጢስ እሳት ዉሀ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የሚሰጡ ሚክስሮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማስጠገን ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ማንኛውም በዘርፉ የተሰማሩና በጨረታዉ መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ በጨረታዉ መሳተፍ ይችላሉ፡፡

ተ.ቁ የእቃዉ  (የጥገናዉ) አይነት የጨረታ ማስከበሪያ ምርመራ
1 750 ሊትር ሚክሰር ጥገና ብር 20,000 ኢንጅን እና ጊር ቦክስ ጥገና
  1. ተጫራቾች የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የቲን ሰርተፊኬት ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  1. ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን ከቀኑ 9፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 9፡30 ባሕር ዳር ከተማ አባይ ማዶ ቴዲ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ጎን በሚገኘው ዋናዉ መ/ቤት ተጫራቾች እና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በኩባንያችን አባይ ማዶ ቴዲ የአሸከርካሪዎች ማሰልጠኛ ጎን በሚገኘው ዋናዉ መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 011 ግዥ መምሪያ በነጻ (ያለ ክፍያ) መዉሰድ ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከላይ በተቀመጠዉ በሰንጠረዥ መሰረት ተቀባይነት ባላቸው የአፈጻጸም ዋስትናዎች (ቢድ ቦንድ) በባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) ማስያዝ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታዉ ለመሳተፍ የሚያወጡት ወጪ በተጫራቹ የሚሸፈን ይሆናል፡፡
  5. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸዉን እና የጨረታ ማስከበሪያዉን በተለያየ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች ለሚያቀርቡት ለእያንዳንዱ የጥገና ነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ በትክክል ሞልተው በግልጽ ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
  6. ይህ ጨረታ በኩባንያችን የግዥ መመሪያ PR-03/2017 መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
  7. ኩባንያው በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተገለፀዉ መጠን 25 በመቶ ቢጨምር ወይም ቢቀንስ የጨረታ አሸናፊዉ ዉል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል፡፡
  8. የጨረታዉ አሸናፊ አሸናፊነቱ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ5 የስራ ቀናት ዉስጥ የጠቅላላ ዋጋዉን 10 በመቶ የዉል ማስከበሪያ ያለቅድመ ሁኔታ ለገዥ የሚከፈል (Unconclitional Bank Guarantee) በማሰራት ዉል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል፡፡
  9. የማቅረቢያ ጊዜ (የጥገና ጊዜ ) እንደ አስፈላጊነቱ በስምምነት የሚወሰን ይሆናል፡፡ የአቅራቢዎች ዋጋ ቢያንስ ለ90 ቀናት ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ፀንቶ መቆየት አለበት፡፡
  10. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. ማሳሰቢያ፡- እንደ ኩባንያችን ፍላጎት ዉድድሩ በሎት ወይም በእያንዳንዱ እቃ ነጠላ ዋጋ መሠረት ሊሆን ይችላል፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 058 220 48 26 /058 320 25 48 ወይም በፋክስ ቁጥራችን 058 220 48 30 መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ጢስ እሳት ዉሃ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር

ባሕር ዳር

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here