የቡሬ ከተማ አስተዳደር መሬት ጽ/ቤት የከተማ ቦታ ስለመያዝ በደነገገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 መመሪያ ቁጥር 01/2005 መሰረት በ2018 በጀት ዓመት 2ኛ ዙር ጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፦
- የጨረታ ሰነድ ቢሮ ቁጥር 12 በመምጣት የማይመለስ 400 (አራት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ዓይነት መደበኛ
- የጨረታ ሰነድ መግዣ ቀን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡00 ብቻ ይሆናል፡፡
- የጨረታው ሰነድ መሸጫ ጊዜ የሚያልቀው በ10ኛው ቀን በ11፡00 ነው፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው በ11ኛው ቀን ቡሬ ከተ/አስ/ር/መ/ጽ/ቤት ግቢ ከ3፡30 እስከ 4፡00 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም ባይገኙም በቡሬ ከተ/አስ/ር/መ/ጽ/ቤት ውስጥ ይከፈታል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም ሲፒኦ በባንክ የተረጋገጠ የገንዘብ ክፍያ ትዕዛዝ ለድርጅት 5 በመቶ ለመኖሪያ 5 በመቶ በማቅረብ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የተያዘ ገንዘብ አሸናፊው ከተለየ በኋላ የሚመለስ ይሆናል፡፡
- የግንባታ ደረጃ ለድርጅት G+2 እና ከዚያ በላይ ለመኖሪያ G+0 ከዚያ በላይ የቦታው አገልግሎት በእያንዳንዱ ምድብ ከሰነዱ ጋር በሚሸጠው ሰነድ ሰንጠረዥ ላይ የተቀመጠው ይሆናል፡፡ ለጨረታ የወጣው የቦታ ብዛት ድርጅት 05 መኖሪያ 25 ጠቅላላ ድምር 30 ነው፡፡
- በዚህ ያልተገለፀ ሀሳብ ካለ በአዋጁ ቁጥር 721/2004 መሰረት የሚስተናገድ ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 774 16 23 /058 774 03 66 ደውለው ማግኘት ይችላሉ፡፡
የቡሬ ከተማ አስ/ር መሬት ጽ/ቤት

