የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት በ2018 ዓ/ም በጀት አመት በመደበኛ በጀት ለት/ቤቱ የሚስፈልጉ ግብዓቶች ሎት1. ለምግብ አገልግሎት የሚዉል የተዘጋጀ በርበሬ፣ የተዘጋጀ ሽሮ፣ ጤፍ ወዘተ…፣ሎት2. ማገዶ እንጨት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዠዉ መጠን ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ) ብር በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት)ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ በጨረታ ሰነዱ ላይ የተጠቀሱትን የሚመለከታቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ የእቃዎች አይነት እና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ከ1-2 ሎት ድረስ ከቢሮ ቁጥር 6 በመቅረብ የማይመለስ ብር 200 ወይም በባንክ በተመሰረተ (ስፒኦ) ማቅረብ ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን አንድ ነጥብ አምስት ዋስትና (ቢድ ቦንድ) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሰ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታው ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም ወጥ በሆነ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጂ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት ግ/ን/አ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 8 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ተዘግቶ በእለቱ በ4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል 16ኛው ቀን የስራ ካልሆነ ወደ ቀጣዩ የስራ ቀን ይተላለፋል፡፡
- ጨረታው በእያንዳንዱ ፍላጎት በተናጠል ዋጋ ነው፡፡
- አሸናፊው በገባው ውል መሰረት እቃዎችን እስከ ተቋሙ ንብረት ክፍል የማድረስ ግዴታ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ ከተዘረዘረዉ ግዥ መጠን 20 በመቶ ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 08 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 033 111 4684 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት

