ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
22

የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት 2018 በጀት አመት 1ኛ. የጽዳት ዕቃዎች እንዲሁም 2ኛ. የተሽከርካሪ መኪኖች እና የጀኔሬተር መለዋወጫ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ውል በመያዝ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ፡-

  1. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገበ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሣተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው በታሸገ በፖስታ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ነገር ግን ከላይ ከ1-3 የተጠቀሱትን ያላቀረቡ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ ይሆናሉ፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል በግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት  3ኛ ፎቅ ዋና ገንዘብ ያዥ ቢሮ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በመሙላት በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ በግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በግዥና /ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ከመክፈቻ ቀንና ሰዓት በፊት ማስገባት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) ከሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  8. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ከሚያዚያ 19/2018 ዓ/ም እስከ ግንቦት 03/2018 ዓ/ም ድረስ ለተከታታይ 15 ቀን የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን ግንቦት 04/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 3፡30 ተጫራቾች ወይም  ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና /ንብ/አስ/ቡድን  ቢሮ  ይከፈታል፡፡ ይህ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በዚሁ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥና ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09 08 64 99 67 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአማራ  ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት

ባሕር ዳር

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here