በአፈ/ከሳሽ ወ/ሮ ማለፊያ መኮነን እና በአፈ/ተከሳሽ ዝግጁ መኮነን መካከል ስላለው የገንዘብ የአፈጻጸም ክስ ክርክር ጉዳይ በዕድውሃ ከተማ ቀበሌ 02 በምሥራቅ መንገድ፣ በምዕራብ መኮነን ፈንታ፣ በሰሜን መኮነን ፈንታ እንዲሁም በደቡብ አንዳርጌ ከበበው የሚያዋስነው 170.99 ካሬ ሜትር የሆነ የአፈ/ተከሳሽ ቤት በመነሻ ዋጋ ብር 1,967,655.36 (አንድ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባት ሽህ ስድስት መቶ ሃምሳ አምስት ከሰላሳ ስድስት ሳንቲም) በማድረግ ጨረታው ከሐምሌ 06/2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም በጋዜጣ በማዋል ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡00 እስከ 6፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ በጨረታ ስለሚሸጥ መጫረት የሚፈልጉ ሁሉ በጨረታው ቀንና ሰዓት በቦታው በመገኘት መጫረት የሚችሉ ሲሆን የጨረታው አሸናፊ የአሸነፈበትን 1/4ኛውን ይዞ የሚቀርብ መሆኑንና አሸናፊው ከስመ ንብረት ዝውውር ጋር የተያያዙ ወጭዎችን የሚሸፍን መሆኑን እና ውጤቱን ለነሐሴ 07/2018ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ለተያዘው ቀጠሮ በፁሁፍ እንዲቀርብ ሲል ፍ/ቤት አዝዟል፡፡
የሸበል በረንታ ወረዳ ፍ/ቤት

