ማልኮልም ኤክስ

0
197

በአሜሪካ የተወለደው ማልኮልም
ኤክስ ለጥቁር ህዝቦች እኩልነት እና ነጻነት
በቁርጠኝነት ሲታገል ኖሮ ሲታገል ባለበት
የተሰዋ ጥቁር ጀግና ነው። ታዲያ ይህ ጀግና
የተገደለው ዛሬ 59 አመት በፊት ልክ በዚሁ
ሳምንት የካቲት 13 ቀን 1957 ዓ.ም ነበር።
ማልኮልም በእስልምና መንፈሳዊ
አስተማሪ እና ጥቁር አፍሪካዊ አሜሪካውንን
ዘር መድልኦ እና ጭቆናን የሚታገል
ጥቁር ህዝብ መብት ተከራካሪ ነበር።
ማልኮም በህይወት ዘመኑ ለጥቁር ህዝብ
የአሜሪካ መንግስት የሚደርስባቸውን
በደል በአደባባይ ይታገል ነበር። በጊዜው
በየጎዳናው የሚደረጉ ሰላማዊ ሰልፎችን እና
ተቃውሞዎችን ሲያስተባብር እና ሲመራ
ነበር፤ ማልኮልም ለጥቁር ህዝብ መብት
ሲታገል ስለነበር መንግስት በአድራጎቶቹ
ደስተኛ አልነበረም። በመሆኑም
አለመግባባቱ እያደገ ሄዶ ለሞቱ ምክንያት
እስከመሆን ደረሰ። በዚህ እለትም ነበር
ንግግር እያደረገ ባለበት ባልታወቁ ሰዎች
የተገደለው።

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here