በፍርድ ባለመብት አለልኝ ሽፈራው እና በፍርድ ባለ እዳ አሰፋ ሽፈራው መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ የባለ እዳው መኖሪያ ቤት የሆነውን በፍኖተ ሰላም ከተማ ቀበሌ 02 በምሥራቅ አለልኝ ፀሐይ፣ በምዕራብ ሽፈራው ገሰሰ፣ በሰሜን ውዴና አሳየ እንዲሁም በደቡብ መንገድ የሚያዋስነው 700 ካሬ ሜትር ቦታ የሚገኘውን ቤት በመነሻ ዋጋ 1,615,355.62 /አንድ ሚሊየን ስድስት መቶ አስራ አምስት ሺህ ሦስት መቶ ሃምሳ አምስት ብር ከስልሳ ሁለት ሣንቲም/ ሆኖ ስለሚሸጥ መግዛት የምትፈልጉ ተጫራቾች ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ለሆነው ቀጠሮ ከጠዋቱ ከ3፡00 እስከ 6፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ በቦታውና በሰዓቱ ተገኝቶ መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን አሸናፊው እንደታወቀ ከሽያጭ ገንዘብ ውስጥ በሞዴል 85 ቢቻል ሙሉውን ካልተቻለ ¼ ኛውን በምዕ/ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአማራ ባንክ የሚያሲዙ መሆኑን ፍርድ ቤቱ ያሣውቃል፡፡