ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
138

በምስራቅ ጎጃም ዞን በሉማሜ ከተማ አስተዳደር የሉማሜ ከተማ መጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት የተለያዩ የውሃ እቃዎችን /ቆጣሪ፣ ቧንቧና መገጣጠሚያ/ በግልጽ ጨረታ በጋዜጣ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፡-

  1. በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  4. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና ሌሎች የሚመለከታቸው ማስረጃዎችን ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከሚገዙት የጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 150.00 / አንድ መቶ ሃምሳ ብር/ ብቻ በመክፈል ቢሮ ቁጥር 02 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ሁለት በመቶ /በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ.ኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጁዎች ዋና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በጽ/ቤቱ በገ/ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ወይም ቢሮ ቁጥር 02 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ16/07/2016 ዓ.ም እስከ 30/07/2016 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በገ/ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ክፍል ቢሮ ቁጥር 02 በ30/07/2016 ዓ.ም የጨረታ ሳጥኑ 3፡00 ላይ ታሽጎ 4፡00 ላይ ይከፈታል፡፡
  11. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 02 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 772 04 65/ 0645 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  13. መሥሪያ ቤቱ የጨረታውን ሃያ አምስት በመቶ የመቀነስ ወይም የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  14. ከተጫራቾች ተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብር /withhold tax/ ከግዥው ዋጋ ላይ የሚቀነስ ይሆናል፡፡
  15. አሸናፊው ማሸነፉ ከተነገረበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ጽ/ቤት ድረስ በመምጣት ውል መያዝ አለበት፡፡
  16. አሸናፊው ውል ሲይዝ የውል ማስከበሪያ አስር በመቶ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርበታል፡:
  17. አሸናፊው ያሸነፈውን እቃ ጽ/ቤቱ ድረስ ማቅረብ አለበት፡፡
  18. አሸናፊው የሚለየው በሎት ነው፡፡

የሉማሜ ከተማ መጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here