ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
152

በአብክመ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሻሁራ ከተማ አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት ለሴ/መ/ቤቶች አግልግሎት የሚውሉ ሎት 1. የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እና ሎት 2. የጽሕፈት መሳሪያዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን  እንገልፃለን፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚረጋግጥ የምስክር ወረቀት ያላቸው፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ  ድምር ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ)፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስና ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በመሥሪያ ቤት የገቢ ደረሰኝ  /መሂ-1 /ገቢ በማድረግ  የደረሰኙን ፎቶ ኮፒ  ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች ከተ.ቁ 1-4 ድረስ የተዘረዘሩትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሁሉም የእቃ ዓይነቶች ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  7. የጨረታ ሰነዱን ከሻሁራ ከተማ አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን የማይመለስ 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ማግኘት ይቻላል፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በፖስታ በማሸግ በሻሁራ ከተማ አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት  ከ16/07/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 30/07/2016 ዓ.ም  አየር ላይ ይውላል በ16ኛው ማለትም 01/08/2016 ዓ.ም የጨረታ ሳጥኑ አስከ ሚታሸግበት  አስከ 4፡00 የጨረታ ሰነድ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሻሁራ ከተማ አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጐ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው  ባይገኙም በመመሪያው መሰረት የጨረታ አከፋፈት ስርዓት ተገዥ ሆነው በሻሁራ ከተማ አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ይከፈታል፡፡
  10. መሥሪያ ቤቱ የጨረታ አሸናፊው ላይ ሃያ በመቶ የመቀነስ ወይም የመጨመር መብት አለው፡፡
  11. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኙ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. በተጫራቾች መመሪያ ይዘት ላይ ምንም ማሻሻያ ማድረግ አይቻልም፡፡
የሻሁራ ከተማ አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here