ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
160

በአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን በ2016 በጀት ዓመት ለኮሚሽኑ አገልግሎት የሚውሉ የተሽከርካሪ መለዋወጫ እና ጎማ  በነጠላ ዋጋ አወዳድሮ ከአሸናፊው ድርጅት ጋር ውል በመያዝ መግዛት ይፈልጋል:: ተወዳዳሪዎች የሚከተሉትን መስፈርቶች ይኖርባቸዋል፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድና የንግድ ምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ::
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉና ክሪላንስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ::
  3. የግዥ ኤጄንሲ የምዝገባ ወረቀት (የአቅራቢነት) የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ እና ቅጣት የሌለባቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል::
  4. ከ200,000.00/ከሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ለሚጫረቱ ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ በደንብ ሊነበብ የሚችል ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ይኖርባቸዋል::
  5. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 የሥራ ቀናት ውስጥ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን አብክመ ፖሊስ ኮሚሽን 1ኛፎቅ ቢሮ ቁጥር 128 መውሰድ ይችላሉ::
  6. ተጫራቾች በገዙት ሰነድ መሰረት የሚወዳደሩበትን ዋጋ በመሙላትና በእያንዳንዱ ገፅ ላይ ፊርማ እና የድርጅቱን ማህተም ዋናውንና ኮፒውን በተለያየ ፖስታ ሆኖ በአንድ ፖስታ በማጠቃለል ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
  7. ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሎት የጨረታ ማስከበሪያ በአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ስም በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ በማዘጋጀት ከዋናው ሰነድ ጋር በፓስታ በማሸግ መስገባት ይኖርባቸዋል::
  8. የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን የሚከፈት ይሆናል::  ቀኑ የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል::
  9. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  10. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በኦርጅናል ሰነዱ ላይ ብቻ በእያንዳንዱ ላይ ቫትን ያጠቃለለ ዋጋ ማቅረብ አለባቸው::
  11. ተጫራቾች ይፋ በሚደረገው ውጤት ቅሬታ ካላቸው በ7 ቀናት ውስጥ ቅሬታቸውን የማቅረብ መብት አላቸው::
  12. ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርበው የጨረታ ሰነድ ስርዝ ድልዝ ኖሮት ካልተፈረመ ፍሉድ ተጠቅሞ በጉልህ የማይነበብ ከሆነ ከውድድር ውጪ ይሆናል::

የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here