በአፈ/ከሣሽ ፀደይ ባንክ ነገር ፈጅ ሙሉጌታ አስራት እና በአፈ/ተከሣሾች 1ኛ አገረ ደመቀ፣ 2ኛ እሴት አዲስ፣ 3ኛ አዲሴ ሰጠ፣ 4ኛ አድማሱ ጌታቸው፣ 5ኛ ወይንሸት ዓለምነው፣ 6ኛ ዓለሚቱ አያሌው፣ 7ኛ ሲሳይ መኮነን፣ 8ኛ ምላሹ አዲሴ፣ 9ኛ ደስታ ወንድምነው እና 10ኛ የማታው አምባው ተቃውሞ አቅራቢዎች እነ ተስፋ አገኘሁ በቁጥር ሦስት ሰዎች መካከል ስላለው የገንዘብ አፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ የ7ኛ አፈፃፀም ተከሳሽ ሲሳይ መኮነን የሆነውን ቤት በእስታይሽ ከተማ በምሥራቅ በሪሁን ጫኔ፣ በምዕራብ ቤተክህነት፣ በሰሜን መንገድ እና በደቡብ የራሳቸው ትርፍ ቦታ ተዋስኖ የሚገኘው ቆርቆሮ ቤት የመነሻ ዋጋ ሳይጠብቅ ከፍተኛ ዋጋ ለሚያቀርብ ተጫራች በሃራጅ ጨረታ እንዲሸጥ ፍ/ቤቱ አዟል፡፡ በመሆኑም የጨረታ ማስታወቂያው ከግንቦት 19 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ሰኔ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ለ30 ቀናት አየር ላይ ቆይቶ ጨረታው ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ድረስ ይካሄዳል፡፡ ስለዚህ በጨረታው መሳተፍ ወይም መግዛት የምትፈልጉ ቤቱ በሚገኙበት በእስታይሽ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ቅጥር ግቢ በመገኝት መግዛት ወይም መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን የጨረታው አሸናፊ ያሸነፈበትን ¼ ኛው ወይም ሃያ አምስት በመቶ ለሐራጅ ባይ ባለሙያ ወዲያውኑ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡