የሰ/ወሎ ዞን ማረ/ቤቶች መምሪያ ከሃምሌ 1/2016 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ለ 1 አመት የሚቆይ ሎት1. ሰርገኛ ጤፍና የተከካ በቆሎ፣ሎት2. ፊኖ ነጭ የዳቦ ዱቄት፣ሎት 3.ምጥን ሽሮና በርበሬ እንዲሁም የባልትና ዉጤቶች የሚያቀርቡ ነጋዴዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸዉ፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በዚሁ የስራ መስክ ለመሰማራት የተመዘገቡ፡፡
- በስማችዉ የታተመ ደረሰኝ ሊኖር ይገባል፡፡
- የሚሞላዉ ዋጋ ከብር 200‚000.00(ሁለት መቶ ሽህ ) በላይ ስለሆነ ተጫራቾች ቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
- የጨረታው ማስታወቂያ በአየር ላይ የሚቆይበት ጊዜ ከ26/09/2016 እስከ 10/10/2016. ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ብቻ ነዉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 1 በመቶ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ ሲፒዩ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ከ26/09/2016 እስከ 10/10/2016 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት ከመ/ቤቱ ዋና ገንዘብ ያዥ የማይመለስ ብር 50.00 /ሃምሳ ብር / በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታዉን ሰነድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማድረግ እስከ ሰኔ 11/2016 ዓ.ም ከቀኑ 3፡30 ድረስ ቢሮ ቁጥር 2 በተዘጋጀዉ ሣጥን ማስገባት አለባቸዉ፡፡ ጨረታዉ በዚሁ ቀን ከቀኑ 3፡30 ላይ ታሽጎ 4፡00 ላይ የጨረታው ባለቤቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ያሸነፋትን አቅርቦቶች በሙሉ በራሳቸዉ ወጭ መ/ቤቱ ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነድ ላይ ሙሉ አድራሻ፣ ማህተም ፊርማና ሌሎችን ማስረጃዎች አሟልተዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
- በጨረታዉ የሚቀርቡ አቅርቦቶች በሙሉ ጥራታቸዉን የጠበቁ መሆን አለባቸዉ፡፡
- የጨረታ አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች የዉል ማስከበሪያ 10በመቶ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- የበለጠ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 033-331-1240/0010 ወይም 0920784565 በመደወል ወይም በአካል ወደ ቢሮው በመምጣት መጠየቅ ይችላሉ፡፡