በአፈ/ከሣሽ ጋሻው በቀለ እና በአፈ/ተከሣሽ ብርሃኔ ዳምጤ መካከል ስላለው የአፈፃፅም ክስ ክርክር ጉዳይ ንብረትነቱ ብርሃኔ ዳምጤ የሆነው ኮድ-3-17629 አማ አባዱላ መኪና ሚኒባስ የሆነ በመነሻ ዋጋ 354,159.00 /ሶስት መቶ ሃምሳ አራት ሺህ አንድ መቶ ሃምሳ ዘጠኝ ብር/ በሆነ መነሻ ዋጋው በሐራጅ እንዲሸጥ ፍ/ቤቱ አዝዟል:: በመሆኑም የሐራጅ የጨረታ ማስታወቂያው ለ30 ቀናት በአየር ላይ ቆይቶ ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ድረስ ጨረታው ይካሄዳል:: ስለዚህ በጨረታ መግዛት የምትፈልጉ መኪናው በሚገኝበት ባሕር ዳር ከተማ በላይ ዘለቀ ክፍለ ከተማ 4ኛ ፖሊስ ጣቢያ በመገኘት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የጨረታ አሸናፊው ያሸነፈበትን ¼ ኛውን በሞ/85 ማስያዝ የሚጠበቅበት መሆኑን ፍ/ቤቱ ያስታውቃል::