ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

0
131

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ለሸዶች የሚያገለግል መካከለኛ ቮልቴጅ ኬብል በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይገልፃል፡፡

  1. የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና በዘርፉ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የዕቃዎች ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከኮርፖሬሽኑ ግ/ፋ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ገንዘብ ያዥ ክፍል 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 09 ሰነዱን ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ 6,000.00 /ስድስት ሺህ ብር/ ብቻ ወይም በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ መሥሪያ ቤቱ ገንዘብ ቤት ገቢ በማድረግ ደረሰኝ ኮፒ በማድረግ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋናና ቅጂ በማለት በጥንቃቄ በማሸግ አረጋዊያን ህንጻ ከሚገኘው ኮርፖሬሽኑ ግ/ፋ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 09 ውስጥ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሠዓት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 20 ተከታታይ የካሌንደር ቀናት እስከ 11፡30 ድረስ መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአብከመ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ግ/ፋ/ንብ/ አስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ውስጥ በ21ኛው ቀን 3፡30 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፤ ሆኖም 21ኛው ቀን እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ጠዋት 3፡30 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡
  10. የጨረታው አሸናፊ የሚለየው በድምር ዋጋ ይሆናል፡፡
  11. አሸናፊው ድርጅት ኬብሉን በስፔስፊክሽኑ መሰረት መሆኑን በባለሙያ ካረጋገጠ በኋላ ከኮርፖሬሽኑ ንብረት ክፍል በማምጣት ገቢ ማድረግ አለበት፡፡
  12. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ አብክመ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ግ/ፋ/ንብ/አስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ድረስ በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 320 47 67 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአብከመ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here