ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
130

በደቡብ ጎንደር ዞን የበጌምድር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ለ2017 በጀት አመት በመደበኛ በጀትና በውስጥ ገቢ በጀት የተለያዩ እቃዎችን ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም 1 የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን እቃዎች በጋዜጣ በግልጽ ጨረታ ዘዴ በማወዳደር መግዛት ይፈልጋል፡፡ ሰለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ መሆን አለባቸው፡፡
  2. የንግድ መለያ ቁጥር (ቲን) ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግዥ መጠኑ ከ200,000.00 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ስለሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋገጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
  4. ኮሌጁ ከ20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ በላይ ግዥ ሲፈጽም መንግስት በሰጠው ውክልና መሰረት ሰባት ነጥብ አምስት በመቶ የተጨማሪ እሴት ታክስ ቀንሶ ያስቀራል፡፡
  5. ኮሌጁ ከ10,000.00 /አስር ሽህ ብር/ በላይ ግዥ ሲፈጽም ሁለት በመቶ የዊዝሆልዲንግ ታክስ ቀንሶ ያስቀራል፡
  6. በሰነዱ ላይ የተጠቀሰዉ ቁጥር ብዛት ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
  7. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸዉን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
  8. የሚገዙትን እቃዎች ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ተጫራቾች ይህ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 50.00 (ሀምሳ ብር) ብቻ በመክፈል ከግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ዋና ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 8 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የሞሉትን የእቃዉን ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ የገቢ ደረሰኝ በመቁረጥ ኮፒዉን ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  11. ተወዳዳሪዎች አሸናፊነታቸው ተገልጾላቸው ያሸነፉትን የዕቃ ጠቃላላ ዋጋ አስር በመቶ የውል ማስከበሪ ዋስትና /ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ የገቢ ደረሰኝ በመቁረጥ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  12. ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በመሙላት ዋናዉን ብቻ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 9 በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ድረስ ከቀኑ 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  13. ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ቢገኙም ባይገኙም በግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ክፍል በቢሮ ቁጥር 9 በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛዉ ቀን 4፡00 ታሽጎ በ4፡10 ይከፈታል፡፡
  14. ዉድድሩን በተናጠል የማናማወዳድር መሆኑን እየገለጽን ነገር ግን ተወዳዳሪዎች ሁሉንም እቃዎች ዋጋ መሙላት አለባቸው፡፡
  15. አሸናፊዎች እቃዎቹን ኮሌጅ ድረስ በማጓጓዝ ንብረት ክፍል ገቢ በማድረግ ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  16. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  17. ስለ ጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 10 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 141 00 31 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  18. ተጫራቾች በሌሎች ዋጋ ላይ ተንተርሰዉ ዋጋ ማቅረብ አይችሉም፡፡
  19. አድራሻ ደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን ደ/ታቦር ከተማ (በጌምድር መ/ራን ትም/ኮሌጅ)

የበጌምድር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here