ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
125

የደ/ጐን/አስ/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት ለ2017 በጀት ዓመት ለመቤቱ አገልግሎት የሚዉሉ ሎት 1. ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 2. ህትመት፣ ሎት 3. የፅህፈት መሳሪያዎች ፣ ሎት 4. አላቂ የፅዳት እቃዎች እና ሎት 5. ሌሎች ቋሚ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት እና ለማሳተም ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. ተጫራቾች ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉና በግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የተመዘገቡ መሆን አለባቸው፡፡
  2. ተጫራቾች በዘመኑ ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
  3. በሎት ከጠቅላላ ዋጋ ከ200,000.00 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ከጠቅላላ ዋጋው ላይ 1% ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያቀርቡት በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ደ/ጐን/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 35 በመቅረብ ማስያዝ ይችላሉ፡፡
  6. የጨረታ ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ ከጨረታ ሠነዱ ጋር በፖስታ ውስጥ አሽጐ ማቅረብ ከጨረታ ውድድር ውጭ ይደረጋል ገንዘቡም ቢጠፋ መ/ቤቱ ሊጠየቅ አይችልም፡፡
  7. መ/ቤቱ ለመግዛት የሚፈልገውን እቃዎች አይነት ዝርዝር የያዘ ሠነድ ማስታወቂያዉ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ሶስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 35 በመምጣት እያንዳንዱን የጨረታ ሰነድ በ50.00 (ሃምሳ ብር) በመግዛት መውሰድ ይችላል፡፡
  8. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በመሙላት በታሸገ ፖስታ አድርገው ማስታወቂያዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ቢሮ ቁጥር 35 በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨሬታ ሳጥኑም በ15ኛዉ ቀን 11፡30 ላይ ይታሸጋል፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ተወካዩች ቢገኙም ባይገኙም የጨሬታ ሳጥኑ በ16ኛዉ ቀን 2፡30 ቢሮ ቁጥር 35 ይከፈታል፡፡
  10. አሸናፊ ድርጅት የሚመረጠዉ ወይንም የሚለዩት በሎት ወይንም በጥቅል ዋጋ ነዉ፡፡
  11. አሽናፊ ድርጅት የአሸናፈዉን እቃ ደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ድረስ አጓጉዞ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፡፡
  12. ተጫራጨቾች ሰነድ በሚገዙበት ጊዜ ኦሪጅናል እና ኮፒ ፍቃድ በመያዝ ሰነዱን በአካል ወይንም በህጋዊ ወኪላችዉ አማካኝነት ማቅረብ ይገባቸዋል፡፡
  13. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  14. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0584410386 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

 

የደ/ጐን/አስ/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here