ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
112

የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል ሰ/ምዕ/ሪጅን/ትራ/ሰብ/ኦፕ ጥገና ቢሮ ለድርጅቱ መኪናዎች አገልግሎት የሚውሉ የተሽከርካሪ ጎማዎችን በግልጽ ጨረታ  አወዳድሮ  መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳዳር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር አጠናቀው  የከፈሉበትን  ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የጨረታ ማስከበሪያ የሚመለስ ዋስትና ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም ባንክ ጋራንት ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡/ ከ90 ቀን በታች የሆነ ባንክ ጋራንት ተቀባይነት የለውም/
  4. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ዝርዝር ጉዳዩን የያዘ ሰነድ  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሰ/ምዕ/ሪጅን ትራ/ሰብ/ኦፕሬሽን ከፖሊ ወደ ጋንቢ በሚወስደው መንገድ ከፍትህ ቢሮ አለፍ  ብሎ በሚገኘው ህንፃ 1ኛ. ፎቅ ፋይናንስ ቢሮ በመቅረብ መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ ላይ በግልጽ በመሙላትና የድርጅቱን ማህተም በመምታት ኦርጅናሉንና ኮፒውን በተለያየ ፖስታ በማድረግ እንዲሁም የተወዳደሩበትን ከፖሰታው ላይ በትክክል በመግለፅ ሁለቱንም ፖስታዎች በአንድነት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ  ከወጣበት ከታህሳስ 14 /2017 ዓ.ም እስከ 03/05/ 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት 15/አስራ አምስት /ተከታታይ የስራ  ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት  ለዚሁ ጨረታ ለማገልገል በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ  በመቅረብ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  6. ጨረታው በ15ኛው የስራ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት/ባይገኙም ከቀኑ 8፡30 በኢትዬጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ስርዝ ድልዝ ያለበት የጨረታ ሰነድ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
  7. ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0582266509/0582220829 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  8. አሸናፊው ተጫራች ከመስሪያ ቤቱ ጋር ማሸነፉ በተገለፀለት  በ5 ቀን ውስጥ ውል መያዝ ይጠበቅበታል፡፡
  9. ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል ሰ/ምዕ/ሪጅን/ትራ/ሰብ/ኦፕ ጥገና ቢሮ

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here