ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
97

የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት በሥሩ ለሚገኙ ሴ/መስሪያ ቤቶች በ2014 የበጀት ዓመት ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ እና ሎት 2 የስፖርት ትጥቅ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን/ ያላቸው፡፡
  4. የግዥ መጠን 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ በተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚገዙ ዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ክጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን 14/04/2017 ዓ.ም እስከ 2/05/2017 ዓ.ም የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የማይመለስ00 /ሃምሳ ብር/ በመክፈል ቢሮ ቁጥር 26 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የጠ/ድምር አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከዋና ገ/ያዥ በደረሰኝ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በ2 ኮፒ በመሙላት የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ኦርጅናል ሰነዱ ውስጥ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቢሮ ቁጥር 35 የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ስዓት እስከ 02/05/2017 ዓ.ም 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 03/05/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ቢኖሩም ባይኖሩም ይክፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፈልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 35 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 817 00 86 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  13. መሥሪያ ቤቱ የጨረታ ውጤቱን በጠቅላላ ድምር ውጤት ያያል፡፡
  14. አሸናፊ ድርጅት ንብረቱን ደ/ከ/አስ/ገን/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 34 ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይኖርባቸዋል፡፡
  15. ተጫራቾች በመጫረቻ ሰነዶቻቸው ላይ ሙሉ ስማቸውን ፊርማቸውን እና የድርጅቱን ማህተም ማድረግ አለባቸው፡፡

የደባርቅ ከተማ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር /ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here