በድጋሜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
122

በምዕራብ ጎንደር ዞን የመተማ ጠቅላላ ሆስፒታል ለ2017 ዓ.ም  በጀት አመት ለመ/ቤቱ  አገልግሎት የሚዉል  ሎት 01 የኤሌክትሮኒክስ እቃ ፣ሎት 2 ፈርኒቸር  እንዲሁም ሎት 3 የኤሌክትሮኒክስ ጥገና  በግልጽ ጨረታ አዳድሮ ለመግዛት እና ለማስጠገን  ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች  የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  2. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  3. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው  ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. የሚገዙ እና የሚጠገኑ እቃዎች አይነት እና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ 50.00 /ሀምሳ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በሥራ ስዓት በምእራብ ጎንደር ዞን መተማ ጠቅላላ ሆስፒታል ግዥ እና ፋይናንስ ቢሮ መግዛት ወይም ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት የእቃው ጠቅላላ ዋጋ አንድ  በመቶ ባንክ በተረጋገጠ ክፍያ ወይም ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው ወይም በጥሪው  ማስያዝ ይችላሉ፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናል  እና ኮፒውን በተለያዩ ፖስታ ለየብቻ በመለየት በጥንቃቄ  በታሸገ  ፖስታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ጨረታውን  በጋዜጣ ታትሞ አየር ላይ ከዋለበት ከ 05/05/2017 እስከ 19/05/2017 ዓ.ም ጀምሮ መውሰድ እና መመለስ የሚችሉ ሲሆን በ16ኛው ቀን ማለትም በ 20/05/2017  ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በምእራብ ጎንደር ዞን መተማ ጠቅላላ ሆስፒታል  ግዥ እና ፋይናንስ ቢሮ በግልጽ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  8. አሸናፊው የሚለየው በሎት በጥቅል እቃ ዋጋ ሲሆን መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በነጠላ ዋጋ አሸናፊ መለየት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  9. አሸናፊ ድርጅቱ በምዕራብ ጎንደር ዞን ፍትህ  መምርያ ቀርቦ ውል መውሰድ የሚችልና እቃዎችን መተማ ጠቅላላ  ሆስፒታል  ባለው ንብረት መጋዘን በዝርዝር ማስረከብ የሚችል፡፡
  10. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 331 03 54 /058 331 01 75 ደውለው ማግኘት ይችላሉ፡፡
  11. አሸናፊው እቃውን ማቅረብ ያለበት በጨረታ ሰነዱ ላይ የተሰጠውን ሞዴል እንጂ ሥርዝ /ድልዝ ሌላ ተመሳሳይ እቃ ማቅረብ አይችልም፡፡
  1. መ/ቤቱ ከተጠየቀው ጠቅላላ እቃ አቅረቦት ሃያ በመቶ ከፍ ወይም ዝቅ ማለት ይችላል፡፡
  1. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኝ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የመተማ ጠቅላላ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here