የመሬት ሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ

0
105

ዳንግላ ከተማ አስተዳደር ከ/ል/መ/ል/ጽ/ቤት የመሬት ልማት ባንክ ቡድን የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገው አዋጅ መሠረት ለመኖሪያ እና ለንግድ አገልግሎት የተዘጋጁ ቦታዎችን 1ኛ/ዙር በግልጽ መደበኛ ጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መጫረት የሚፈልጉ ማንኛውም ሰው ከ05/05/2017 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የቦታውን ዝርዝር መረጃ እና ለጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር ለድርጅት ሆነ ለመኖሪያ 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ዳንግላ ከተማ አስ/ከ/ል/መ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 07 ድረስ በመምጣት ዘወትር በሥራ ስዓት ሰነድ መግዛት እና መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሣውቃለን፡፡ የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ እና መሸጫ ጊዜ ከ05/05/2017 ዓ/ም  እስከ ጥር 14/05/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡00 ይሆናል፡፡

  1. ጨረታው የሚዘጋው ጥር 14/05/2017 ዓ.ም ከቀኑ በ11፡00 ሁሉም የጨረታ አስፈፃሚ ቡድን አባላት እና አግባብ ያለው አካል የሚሰይማቸውን ታዛቢዎች በተገኙበት ይሆናል፡፡
  2. ቦታውን መጎብኘት ለሚፈልጉ ተጫራች በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚገለፀው መርሃ ግብር መሠረት የምናስጎበኝ ይሆናል፡፡
  3. ጨረታው የሚከፈተው ጥር 15/2017 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአገው ምድር አዳራሽ ይሆናል፡፡
  4. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ በዳንግላ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ቦታዎች በሚለጠፋ ማስታወቂያዎች እና ቢሮ ቁጥር 6 ወይም በስልክ ቁጥር 058 221 00 54 ወይም 058 221 00 06 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  5. መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ዳንግላ ከተማ አስተዳደር ከ/ል/መ/ል/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here