በአፈ/ከሳሽ ጌች ግሮሰሪ እቁብ ማህበር ሰብሳቢ አቶ አለኸኝ ልየው እና በአፈ/ተከሳሽ እነ ወ/ሮ በላይነሽ አለነ እና 3ቱ ራሳቸው መካከል ስላለው የገንዘብ ክርክር ጉዳይ፤ በእንጅባራ ከተማ ቀበሌ 05 አዋሳኝ በምእራብ እና በደቡብ መንገድ፣በሰሜን ዳኛው እምሬ እና በምስራቅ ጋሻው ደሳለው መካከል ተዋስኖ የሚገኘው እና በአፈ/ተከሳሽ ወ/ሮ በላይነሽ አለነ ባለቤት በአቶ መልካሙ አሸነፍ ስም ተመዝግቦ የሚገኘው የመኖሪያ ቤት በመነሻ ዋጋ 1,920,000.00 / አንድ ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ሀያ ሽህ / ብር ስለሚሸጥ ከጥር12/2017 ዓ.ም እስከ የካቲት 13/2017 ዓ.ም በአየር ላይ ቆይቶ ፤ ጨረታው የካቲት 13/2017ዓ.ም ከ2፡30 እስከ 6፡00 ስለሚሸጥ መጫረት የምትፈልጉ በቦታው እና በሰአቱ ተገኝታችሁ መጫረት የምትችሉ መሆኑን ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡
የባንጃ ወረዳ ፍ/ቤት