ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
74

የእብናት ወረዳ ፍ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ለፍ/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 የጽፈት እቃዎች ፣ሎት 2 ፈርኒቸር  ፣ ሎት 3 ህትመት ፣ ሎት 4 የሌሌክትሮኒክስ ፣ሎት 5 የጽዳት እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው ተመዝጋቢነት የምስክር ወረቀት ያላቸው፡፡
  4. የገዥው መጠን ከ200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. መስረያ ቤቱ በሎት በተናጠል ዋጋ በሞሉት የሚያወዳድር ይሆናል፡፡
  7. ማንናቸውም ተጫራች ከሚወዳደረበት ሎት ውስጥ ሁሉንም ካልሞላ ከጨረታ ውጭ ይደርጋል፡፡
  8. ፍ/ቤቱ በአጠቃላይ እንዲገዛ ካዘዘው እቃዎች ላይ ሃያ በመቶ የመጨመርና የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ይሆናል፡፡
  9. የሚገዛውን እቃ አይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡ ሆኖም ስፔስፊኬሸን ሳይሞላ ክፍት ያደረገ ተጫራች ከጨረታ ውጭ ይሆናል፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ00 /ሃምሳ ብር/ በመከፈል ግ/ፋ/ን/አስ/ቡ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 12 መግዛት ይችላሉ፡፡
  11. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በሚወዳደረበት ብር የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና /በጥሬ ገንዘብ/ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  12. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም በአንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ግ/ፋ/ን/አስ/ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 12 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት አለባቸው፡፡
  13. ጨረታው ከ26/05/2017 እስከ 26/06/2017 ለ1 ወር ተከታታይ ቀን ከቆየ በኋላ በ27/06/2017 ዓ.ም ቀኑ የህዝብ በዓል ከሆነ ተከታታይ ባለው ቀን ከ3:00 በኋላ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  14. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግ/ፋ/ን/አስ/ጉ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 12 ከ3፡00 በኋላ ይከፈታል፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  16. ተጫራቾች ያሸነፏቸውን እቃዎች ከመ/ቤቱ እ/ወ/ፍ/ቤት ድረስ በራሳቸው ትራንስፖርት አጓጉዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  17. አሸናፊው እንደ አስፈላጊነቱ ለ6 ወር ኮንትራት ውል አገልግሎት ሊወስድ ይችላል፡፡
  18. የጨረታው አሸናፊ መሆን የሚችለው በየሎቱ በተናጠል ዋጋ ዝቅተኛ የዋጋ መጠን የሞላ ነው፡፡
  19. የሚያቀርቡት እቃ በተጠየቀው ስፔስፊኬሽን እና በናሙናው መሰረት መሆን አለበት፡፡
  20. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 12 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 440 01 23 ደውለው መጠየቅ ይቻላል፡፡

የእብናት ወረዳ /ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here