ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
100

በወልዲያ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የመንግስት የልማት ድርጅት የሆነው ገነቴ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በ2017 በጀት አመት ለሚገነባው የከሚሴ እናቶች እና ህጻናት ሆስፒታል ህንጻ ግንባታ ፕሮጀክት የሚውል ሎት 1 ሴራሚክና ፎርስሊን ንጣፍ አቅርቦት እና ሎት 2  ለመንገድ ማስዋብ ግንባታ የሚውል ባዞላ/ colour chequered Terarazo) አቅርቦት በዘርፉ ከተሰማሩ ህጋዊና ብቃት ካላቸው ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉና ከዚህ በታች የተጠቀሰውን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. ተጫራች በሥራ ዘርፉ በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ የግር ከፋይነት መለያ ቁጥር /ቲን/ ሰርተፊኬት ያላቸውና የዘመኑን የሥራ ግብር የከፈሉ፣ ሁሉንም ሰነዶቻቸውን ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በፖስታ አሽገው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  2. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ከሞሉት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በተረጋገጠ ሲፒኦ የባንክ ጋራንቲ ዋና /ኦርጅናል/ ዶክመንት ሰነዶች ጋር አያይዘው አብረው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ቼክና ኢንሹራንስ ማቅረብ አይቻልም የተከለከለ ነው ተቀባይነትም የለውም፡፡
  3. ተጫራች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማይመለስ በእያንዳንዱ ሎት ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ወልዲያ ከተማ ጎማጣ በሚገኘው ከኢንተርፕራይዙ ግዥና ፋይ/ንብ/አስ/ር ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡ የጨረታ ሳጥኑ በ15ኛው ቀን 11:00 ላይ ታሽጎ በሚቀጥለው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ላይ በኢንተርፕራይዙ ጽ/ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ከመከፈት አያግደውም፡፡
  4. ክፍያን በተመለከተ በሁሉም ሎቶች በአማካሪዎች የጸደቀ በማቅረብና በጸደቀ ሳምፕል መሰረት ቦታው ድረስ ማቅረብ ሲችሉ ነው፡፡
  5. በጨረታው ቅር የተሰኘ ተጫራች የጨረታ ውጤቱ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ በ5 የሥራ ቀናት ብቻ ቅሬታው ማቅረብ ይችላል፡፡
  6. ማንኛወም ተጫራች ዋጋ ሲሞላ ቫትንና ሌሎች ታክሰን ጨምሮ መሙላት አለባቸው፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መሙላት የተከለከለ ነው፡፡
  8. ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  9. ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 09 13 50 49 72 /09 12 91 82 14 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ገነቴ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here