የመገንዘብ ክህሎትን የሚያሳድገው

0
110

ልጆችን ከአንድ በላይ ቋንቋ እንዲናገሩ ማስቻል፣ በተለይም ለዓዕምሮ ዝግመት ተጠቂዎች የተለያዬ አስተሳሰብ እና አመለካከቶችን ተረድተው የማገናዘብ ዓቅምን እንደሚያሳድግላቸው ሳይንስ ዴይሊ ድረ ገጽ ሰሞኑን አስነብቧል::

በአሜሪካ የሚያሚ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ባካሄዱት ጥናት ከአንድ በላይ ቋንቋ የሚናገሩ ልጆች ስሜታቸውን በመቆጣጠር የተለያዩ ተግባራትን የመፈፀም ዓቅም እንደሚያዳብሩ አረጋግጠዋል::

ልጆችን ከአንድ በላይ ቋንቋ እንዲናገሩ ማስቻል ከማስፈፀም ዓቅም ችሎታ ጋር እንደሚቆራኝ እና ይህም  የዓዕምሮ ዝግመት ምልክቶችን እንደሚያሻሽል ነው ያሰመሩበት – ተመራማሪዎቹ::

በታዳጊዎች ላይ ማህበራዊ የግንኙነት ችግሮች እና የመፈፀም አቅምን መገደብ፣ ተደጋጋሚ ባህሪያትን ማሳየት የመሳሰሉትን ለማሻሻል ዓቅም ይፈጥራል- ከአንድ በላይ ቋንቋ መናገር መቻል::

ከተመረጡ ቤተሰቦች የሚገኙ ከ100 የሚበልጡ ከፊሎቹ የዓዕምሮ ዝግመት (ኦቲዝም) ተጠቂ እና ከፊሎቹ ተጠቂ ባልሆኑ  የጥናቱ ናሙና በተካሄደባቸው ልጆች – ወላጆች ከአንድ በላይ ቋንቋ ተናጋሪ ልጆቻቸው የተገኙ ለውጦችን እንዲመዘግቡ ተደርጓል::

በክትትሉ ከተመዘገቡ ለውጦችም ታዳጊዎቹ የሚከለከሉትን የመግታት፣ የተለያዩ አመለካከቶችን መረዳት የሚያስችላቸውን ደግሞ ለማስቀጠል ዓቅም ማዳበራቸው ነው በማጠቃለያ ውጤትነት የተቀመረው::

በካሊፎርኒያ እና ሎስአንጀለስ ዩኒቨርሲቲ ኘሮፌሰር እና የዓዕምሮ ዝግመት እና ተዛማጅ ጉዳቶች ህክምና ማዕከል ዋና ስራ መሪ ከአንድ በላይ ቋንቋ ተናጋሪነት በታዳጊዎች ላይ አወንታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩ በግኝትነት ነጥሮ መውጣቱን አረጋግጠዋል::

የዓዕምሮ ዝግመት ባለባቸውም ሆኑ ከሌለባቸው ታዳጊዎች ወላጆች በአፍ መፍቻ  ቋንቋም ሆነ በአዲስ ቋንቋ ከመግባባት እንዲታቀቡ  እንደሚያደርጉ ደርሰውበታል:: ለዚህ  ምክንያቱ ሊከብዳቸው ወይም ይጠጥርባቸዋል ከሚል መሆኑን ነው ያረጋገጡት::

በመጨረሻም ታዳጊዎች ከአንድ በላይ ቋንቋ በቤት ውስጥ እንዲናገሩ ማስቻል ጥቅም እንጂ ጉዳት የሌለው መሆኑን በማጠቃለያነት አስምረውበታል- ተመራማሪዎቹ::

(ታምራት ሲሳይ)

በኲር የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም  ዕትም

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here