ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
106

በደ/ጎንደር ዞን የሰዴ ሙጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግን/አስ ቡድን ለ2017 በጀት አመት ሎት 1 ት/ት/ጽ/ቤት ለአዲስ አለም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከደረጃ 7 በላይ ያላቸውን ተጀምሮ የቀረውን ግንባታ በክልል እና በወረዳ በጀት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰገንባት ይፈልጋል፡፡ በመደበኛ በጀት ሎት 2 የጽህፈት መሳርያ፣ ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 4 የጽዳት እቃ እና ሎት 5 የመኪና ጎማ ግዥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡- ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የሚያሟሉ መጫረት የሚችሉ መሆኑን ይገልፃል፡-

  1. በየዘርፉ ህጋዊ ፣ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉና ቲን ካርድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የሞሉት ዋጋ ከ200‚000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከ1-3 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች ሙሉ ስማቸውን ፊርማቸውን አድራሻቸውን በድርጅቱ ስም የተዘጋጀ ማህተም መምታት አለባቸው፡፡
  6. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዱን የማይመለስ ብር 150 /አንድ መቶ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከመ/ቤታችን ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 04 ዘወትር በሥራ ቀን መግዛት ይችላሉ፡፡
  7. የሚገዙ እቃዎችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ /በመሂ1 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ በኋላ አስር በመቶ የውል ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ (በባንክ በተረጋገጠ /ሲፒኦ/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው ለ15 ተከታታይ ቀን ተለጥፎ ይቆያል፡፡
  11. ጨረታው በ16ኛው ቀን በ3፡00 ይታሸጋል፡፡ በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 2 በዚሁ ቀን 3፡30 ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች  (ህጋዊ ወኪሎቻቸው) ጨረታውን ለመክፈት ቢገኙም ባይገኙም ለመክፈት አያስተጓጉልም፡፡
  12. የጨረታ ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡
  13. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
  14. በማስታወቂያ ያልተገለጹ ካሉ በግዥ መመሪያው መሰረት ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  16. የመልካም ሥራ አፈጻጸም መገለጫ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  17. ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ ይደረጋሉ። ለወደፊቱም በመንግስት ጨረታ እንዳይሳተፉ የሚደረጉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
  18. የጨረታ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የማወዳደርያ ሃሳብ ላይ ለወጥ (ማሻሻያ) ማድረግና ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
  19. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 2 ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስ/ቁ 09 18 28 07 69 ደውሎ መጠየቅ  ይቻላል፡፡

የሰዴ ሙጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here