ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

0
125

የመርሳ ከተማ አስተዳደር ከ/መ/ልጽ/ቤት በ2017 በጀት አመት የሚሰሩ መሰረተ ልማት ሥራዎች መካከል ሎት 1 02 እና 03  ቀበሌ ከሞላ ይመር ቤት እስከ ከድጃ ጀማል ቤት ድረስ 850 ሜትር አዲስ ጠጠር መንገድ ሥራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

  1. በዘርፋ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸዉ፡፡
  4. የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. የሥራ ልምድ ማስረጃ በመንግስት የሥራ ቋንቋ በአማርኛ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  6. ደረጃ 5(አምስት) እና በላይ የሙያ ፈቃድ ያለው (ደረጃ 6፣7፣8፣9 አያካትትም)፡፡
  7. የሚጫረቱበት ጨረታ ዋጋ 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ /የቫት/ ተመዝጋቢ ሰርተፊኬት ያላቸዉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት 1 ብር 120,000 /አንድ መቶ ሃያ ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ ገቢ ያደረጉበትን ደረሰኝ ወይም በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ባልተመሰረት የባንክ ዋስትና ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሌተር ኦፍ ክሬድት ከጨረታ ሰነዱ ጋር በፖስታ አያይዘዉ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተጫራቾች በጨረታዉ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-8 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከማጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ዋጋ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ቢሮ ቁጥር 2 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  11. የሥራዉን ዝርዝር መግለጫ ከመጫረቻ ሰነዱ ማግኘት ያችላሉ፡፡
  12. ማንኛውም ተጫራች ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሀሳብን በአንድ ወይም በአንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በመርሳ ገንዘብ ጽ/ቤት በግዥና ፋይናስ ንብረት አስተዳደር ቡድን ወይም በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት 10/06/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 09/07/2017 ዓ.ም ድረስ የጨረታ ሰነዱን መግዛትና ማስገባት ይችላሉ፡፡
  13. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 2 በ31ኛው ቀን በ10/07/2017 ቀን በ3፡00 ታሽጎ በ3፡30 ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታውን ከመክፈት አይስተጓጎልም፡፡ የጨረታ መክፈቻው የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ ሥራ ቀን በተቀመጠው ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
  14. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. ስለጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 2 ወይም 09 14 46 10 24 /09 35 21 25 15 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  16. ተጫራቾች የአሸነፋቱን ሎት የማቴሪያልና የጉልበት ወጪ በተጫራቾች የሚሸፈን ነዉ፡፡
  17. ሥርዝ፣ ድልዝ እና ፍሉድ መጠቀም አይቻልም፡፡ ከጨረታ ዉጭ ያደርጋል፡፡
  18. የጨረታ ዋጋ ጸንቶ መቆያ ጊዜ ጨረታዉ ከተከፈተበት ጊዜ ጀምሮ ለ60 ቀን የጸና ይሆናል፡፡
  19. 3 እና ከዚያ በላይ ተወዳዳሪዎች ከቀረቡ አርቴሚቴክ ዉጤት ልዩነት ከሁለት ነጥብ አምስት በመቶ በላይ ከመጣ ተቀባይነት የለዉም ከ3 በታች ተወዳዳሪዎች ከቀረቡ ከአንድ በመቶ በላይ የአርቲሜቲክ ልዩነት ተቀባይነት የለዉም፡፡

የመርሳ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here