እብናት ወረዳ ገ/ኢ/ል ጽ/ቤት ለእብናት ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል በህበረት 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግቢ ውስጥ G+1 ባለ 10 የመማሪያ ክፍል ለማስገንባት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ሁሉ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፡-
- የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ያላቸው፡፡
- ተጫራቾች ደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ጠቅላላ ዋጋ ድምር ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) በእብናት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ስም በማሰራት ወይም በባንክ የተረጋገጠ የባንክ ጋራንት (በጥሬ ገንዘብ እብናት ወረዳ ገ/ኢ/ል ጽ/ቤት ዋና ገ/ያዥ ገቢ በማድረግ ግቢ የሆነበትን የገቢ ደረሰኝ ከኦርጅናሉ የጨረታ ሰነዱ ጋር ታሽጎ መቅረብ አለበት፡፡
- ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ አድርጎ ኦርጅናል ሰነድ እብናት ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ግዥና/ን/አስ/ቡደን መሪ ቢሮ ቁጥር 06 ባዘጋጀዉ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታዉ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት የመጀመሪያ ቀን አንስቶ ለተከታታይ ለ21 ቀን ዉሎ በ22ኛው ቀን ይከፈታል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች (ህጋወዊ ወኪሎቻቸው) ቢገኙም ባይገኙም በግዥና/ን/አስ ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 06 ጨረታው በወጣ በ22ኛው ቀን 8፡30 ታሻጎ 9፡00 ላይ ይከፈታል፡፡ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ (የህዝብ በዓል ከሆነ) በቀጣይ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ስዓት ይከፈታል፡፡
- አሸናፈዉ ለሥራ በተፈለገበት ስዓት ለ3 ቀናት ተጠብቆ ካልቀረበ በመመሪያ መሰረት መ/ቤቱ እርምጃ የመዉሰድ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ዝርዝር ከሚሞሉበት ሰዓት ሥርዝ ድልዝ ወይም በፍሉድ የጠፋ ከሆነ ከጨረታ ዉጭ ይደረጋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 08 የማይመለስ ብር 500 /አምስት በመቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ደረቅ ቸክ ማስያዝ አይቻልም፡፡
- አሽናፊዉ አሽናፊነቱን እንደተገለፀለት ክ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እብናት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ በመቅረብ የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ውል መዉሰድ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን መሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት አለዉ፡፡
- ጨረታዉ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ 30 ቀን ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 06 በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 058 440 06 06 /218 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የእብናት ወረዳ ገ/ኢ/ል ጽ/ቤት