ለመጀመሪያ እና ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
82

የላይ ጋይንት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ቡድን በ2017 ዓ.ም በጀት አመት በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ምድብ 1  የጽህፈት መሳሪያዎች፣ ምድብ 2  በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን በላይ ጋይንት ወረዳ ከቀበሌ 13 ከአንጠባጥቤ እስከ ደምበጣ ገብርኤል ድረስ ለሚሰራው መንገድ ከደረጃ 5 በላይ የሆኑ ኮንትራክተሮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት እና ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ መወዳደር የሚፈልጉ ማንኛውም ድርጅት መጫረት የሚችሉ መሆኑን እየገለፅን፡-

  1. በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ /ቲን/ ነበር ያላቸው፡፡
  3. የሚያቀርቡት እቃ ከ200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢነትን የማረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ለመንገድ ሥራው የታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳታፍ ከላይ ከ1-4 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚገዙት እቃዎች አይነትና የሚሰራው መንገድ ሥራ ዝርዝር መግለጫ /ሰፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  7. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ለእያንዳንዱ ሰነድ በመክፈል ላይ ጋይንት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ እና ንብረት አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 04 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት የእቃውን እና የመንገዱን ሥራ ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ እና በጥሬ ገንዘብ በመሂ1 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ለእቃዎቹ ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን ኦርጅናልና ቅጅ በማለት በተለያዩ ፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ ላ/ጋ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 04 በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው በ16ኛው ቀን በ3፡30 ይዘጋና በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ላ/ጋ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 04 በ16ኛው ቀን በ4፡00 ይከፈታል፡፡
  11. ለመንገድ ሥራው ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን ኦርጅናልና ቅጅ በማለት በተለያዩ ፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ ላ/ጋ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 04 በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  12. ጨረታው በ22ኛው ቀን በ3፡30 ይዘጋና በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ላ/ጋ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 04 በ22ኛው ቀን በ4፡00 ይከፈታል፡፡
  13. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ጨረታው ከመከፈቱ አይስተጓጐልም፡፡
  14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. አሸናፊው ድርጅት የአሸነፈውን እቃዎች በየፑሉ ማድረስ የሚችል መሆን አለበት፡፡
  16. ከጨረታ ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ ካለ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
  17. ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
  18. ውድድሩ የሚካሄደው በሎት ዋጋ ነው፡፡
  19. በማስታወቂያ ያልተገለፁ ሌሎች ካሉ በግዥ መመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
  20. ከሎቱ ውስጥ ያንዱን ዋጋ ካልሞሉ ከውድድር ውጭ ያደርጋል፡፡
  21. ሥለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ላ/ጋ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 04 ቢሮ ቁጥር 4 ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 058 445 13 99 /058 445 00 05 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

የላይ ጋይንት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here