ከታቀደው በላይ ምርት መገኘቱ ተገለጸ

0
83

በአማራ ክልል በ2016/17 የምርት ዘመን አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ ከ169 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ማግኘት መቻሉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል::

ከሮው የማሕበራዊ ትስስር ገጽ ባገኘነው መረጃ ቢሮው የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን ከዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊዎች  እና ቡድን መሪዎች ጋር በባሕር ዳር ከተማ ገምግሟል:: የቢሮው ምክትል ኃላፊ አጀበ ስንሻው እንደገለጹት ይህ ምርት ሊገኝ የቻለው የዝናብ አጀማመሩ እና ስርጭቱ ለሰብል ልማት ተስማሚ ስለነበር ነው:: እንዲሁም ምርትን ሊያሳድጉ የሚችሉ ግብዓቶችን እና ቴክኖሎጅዎችን አርሶ አደሩ በአግባቡ ስለተጠቀመ ጭምር ነው:: ሰባት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያም ለአርሶ አደሮች ተከፋፍሎ እንደነበር ጠቁመዋል:: ክልሉ የበቆሎ፣ ጤፍ እና  ስንዴ ምርጥ ዘር አቅርቦት ላይም የራሱን ፍጆታ ከመሸፈን ባለፈ ለሌሎች ክልሎች ጭምር መትረፉ ተገልጧል::

በምርት ዘመኑ 169 ሚሊዮን ኩንታል ለማግኜት መታቀዱ  ይታወሳል፤  ከዕቅዱ  በላይ ምርት  መገኘቱንም  የቢሮው  መረጃ   አመላክቷ ል::

(ሳባ ሙሉጌታ)

በኲር የካቲት 17  ቀን 2017 ዓ.ም ዕትም

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here