ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
78

የቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት ለቻግኒ ከተማ አስተዳደር ሴክተር መስሪያ ቤቶች የሚውል የተለያዩ እቃዎች ማለትም ሎት 1 ቋሚ አላቂ እና አላቂ የቢሮ እቃዎች፤ ሎት 2 የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች፤ ሎት 3 የመብራት እቃዎች ፤ ሎት4 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፤ ሎት 5 የእስፖርት እቃወች እና አልባሳት እና ሎት 6 የጽዳት እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል።

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው።
  3. የግዥው መጠን ብር 200,000/ሁለት መቶ ሺህ/ ብር እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች አንድ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
  5. የሚገዙ የዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል።
  6. ተጫራቶች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 250/ሁለት መቶ/ በመክፈል ከቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፤ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ በመግዛት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ሎት 1∙ ቋሚ አላቂ እና አላቂ የቢሮ እቃዎች 10,000/አስር ሽህ/ ብር ፣ ሎት 2∙ የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች 25,000/ሃያ አምስት ሽህ/ ብር ፣ ሎት 3∙ የመብራት እቃወች 5,000.00/አምስት ሽህ ብር/ ፣ ሎት 4∙ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች 10,000/አስር ሽህ ብር /፣ ሎት 5∙ የስፖርት እቃወች አልባሳት 10,000/አስር ሽህ ብር/ እና ሎት 6∙ የጽዳት እቃዎችን 15,000/አስራ አምስት ሽህ ብር ብቻ/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ)፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ /መሂ-1 /ገቢ በማድረግ የደረሰኙን ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ አለባቸው፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች ያሸነፈባቸውን እቃዎች አሸናፊ ተለይቶ ውል ከተያዘ በኃላ በራሱ ወጭ እስከ ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፤ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ ድረስ አምጥቶ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፤ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ  4፡15  ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፤ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ ጨረታው በወጣ በ16ኛው ቀን ከጥኃቱ 4፡15 ታሽጎ 4፡30 ይከፈታል ፡፡
  11. የገዙትን የጨረታ ሰነድ በእያንዳንዱ ገጽ በመፈረም የድርጅቱን ማህተም እና አድራሻ አድርጎ መመለስ አለበት፡፡
  12. ተጫራቶች ለግዥ መመሪያ ተገዥ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
  13. አሸናፊው የሚለየው በሎት በተሞላው ጥቅል ድምር ዋጋ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
  14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቻግኒ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፤ፋይናንስ ንብረት አስ/ ቡድን ቢሮ ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0582251721/0582251631 በመደወል መጠየቅ ትችላላችሁ፡፡

ቻግኒ ከ/አ/ገ/ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here