በድጋሚ የወጣ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
85

የደብረ ማርቆስ አጠ/ስፔ/ ሆስፒታል በ2017 በጀት ዓመት ለሆስፒታሉ አገልግሎት የሚውሉ ለኔትወርክ ኢንስታሌሽን የሚያስፈልጉ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፤ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ።

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የንግድ ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸው፡
  2. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ።
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና / ቢድ ቦንድ / ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 3000 /ሶስት ሽህ/ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ / ሲፒኦ/ ኦርጅናሉን ወይም በጥሬ ገንዘብ የተያዘ ከሆነ የደረሰኞችን ፎቶ ኮፒ ከፋይናንስ ወይም ከዋጋ ማቅረቢያ ፖስታ ውስጥ አስገብቶ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ጨረታው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ 15 ቀን ቆይቶ በ16 ተኛው ቀን ይከፈታል ፡፡
  5. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  6. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሆስፒታሉ የስብሰባ አዳራሽ ይካሄዳል ፡፡
  7. የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት አያግደውም።
  8. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ /ብር  በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አ/ደ/የስ/ሂደት ቢሮቁጥር 4 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ሆስፒታሉ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. የጨረታ ዋጋው ፀንቶ የሚቆይበት ጨረታዉ ከተከፈተበት ቀን አንስቶ የሚቆጠር ዝቅተኛ ቀን ለ40 ቀናት ፀንቶ ይቆያል፡፡
  11. የጨረታ መዝጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለዉጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታዉ ራሳቸዉን ማግለል አይችሉም፡፡
  12. ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ከግ/ፋ/ ን/አ/ደ/የስ/ሂደት በአካል በመገኘት / በስልክ ቁጥር 058 771 22 46 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here