ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
89

የምዕከላዊ ጎንደር አስተዳደር ዞን የምዕራብ በለሳ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓ/ም ለምዕራብ በለሳ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በሴፍትኔት የኑሮ ማሻሻያ በጀት ድጋፍ ለፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች የመስኖ ልማት የውሃ ማሰባሰብ አገልግሎት የሚውል 100 (አንድ መቶ) የውሃ መሳቢያ ሞተር መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ይህን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች /አቅራቢ ድርጅቶች/ እንድትወዳደሩ እየጋበዝን፡- በዚህ መሠረት ለመወዳደር ፍላጎት ያላችሁ ሁሉ በጨረታው መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሠ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ነምበር ያላቸው፡፡
  3. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  4. ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት ቀን 15/07/2017 ዓ/ም እስከ 14/08/2017 ዓ/ም 11፡30 ድረስ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡ ለተከታታይ 30 ቀናት
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ስርዝ ድልዝ ሣይኖረው በመሙላት በሁለት ፖስታ ማለትም ኦርጅናልና ኮፒ በማለት በጉልህ በፖስታው ላይ በመፃፍ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ክብ ምህተም ፣አድራሻ ፣ስልክ ቁጥር መፃፍ አለባቸው፡፡
  6. ጨረታውን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ምዕ/በ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በተዘጋጀው ሣጥን በ15/08/2017 ዓ.ም 3፡30 ታሽጎ በ4፡30 ላይ በግልጽ ይከፈታል፡፡
  7. ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ሥርዝ ድልዝ ካለው ከፊት ለፊቱ ልዩ ፊርማውን ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከጠቅላላ የጨረታ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም በጥሬ ገንዘብ ምዕ/በ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ለእለት ገንዘብ ያዥ ገቢ በማድረግ የገቢ ደረሠኙን ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሠነድ ጋር አያይዞ ከጨረታ ሣጥኑ ከኦርጅናል ሠነድ ጋር ማስገባት አለበት፡፡
  9. አሸናፊው ተጫራች የውል ማስከበሪያ አስር በመቶ የጨረታው ውጤት ከታወቀ የመደን ድርጅት የሚቀርብ በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ በባንክ ቸክና ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ገቢ ያደረጉበትን ኮፒ ማስያዝ የሚችሉ፡፡
  10. ለበለጠ መረጃ ከፈለጉ ምዕ/በ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በስልክ ቁጥር 09 70 11 12 04 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ጨረታው በክልሉ ገ/ኢ/ል/ቢሮ ባወጣው የግዥ መመሪያ የሚተዳዳር ይሆናል፡፡
  13. ሁሉም እቃዎች በጥራት ኮሚቴ ትክክለኛነታቸውን ሲረጋገጥ ገቢ ይደረጋሉ፡፡
  14. የጨረታ ሰነዱን ምዕ/በ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ከረዳት ገንዘብ ያዥ 100 /አንድ መቶ ብር/ መግዛት ይችላሉ፡፡

የምዕራብ በለሳ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here