ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
94

የግዥ መለያ ቁጥር 22/2017

ሱታና ንግድና የማማክር ስራዎች ኢትርፕራይዝ ለተማሪዎች የምግብ አግልግሎት የሚውል ጥራቱን የጠበቀ ቀጭ ቀጭ የሌለው ነጭ ጤፍ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ ፡፡
  1. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ/ ብር በመክፈል ከሱታና ንግድና የማማክር ስራዎች ኢተርፕረይዝ ስራ ክፍል በመዉሰድ ዋጋ በመሙላት የጨረታ ሰነዱን በታሸገ ኢንቨሎፕ /ፖስታ/ የድርጅቱን ስምና ማህተም በማድረግ ኦርጅናልና ኮፒ በማለት ለይቶ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ከጨረታ መዝጊያ ቀን በፊት በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ኢንተርፕራይዙ ብሎክ 2 ቢሮ ቁጥር 203 የምትጫረቱትን የአንዱን ዋጋ በመሙላት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  2. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ተመዝጋቢ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸዉ የሚገዛዉ ዕቃ ከ200,000/ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ የሚሆን ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ አቅራቢ ድርጅቶች ብቻ የሚወዳደሩ ሲሆን ፡፡ የጨረታ አሸናፊዉ ያሸነፈውን ጤፍ የወዛደር ማውረጃ ጭምር ራሱ ችሎ ዩኒቨርስቲዉ ግቢ ድረስ በራሳቸዉ ወጭ  በማቅረብና ማስረከብ አለባቸዉ ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ሲመልሱ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000/አንድ መቶ ሽህ ብር/ ብቻ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በመክፈል ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. የጨረታዉ አሸናፊ የዉል ማስከበሪያ ገንዘብ 10 በመቶ በጥሬ ገንዘብ ወይም /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል ፡፡
  5. የጨረታ አሸናፊዉ ያሸነፋቸዉ ውል መያዝ አለበት፡፡
  6. የጨረታ ሰነዱ ማስገባት የሚጀምረዉ ማስታወቂያዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ሲሆን ጨረታዉ በ16 ኛዉ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ከጥዋቱ 4፡00 ታሽጎ በዚያዉ ቀን በ4፡30 ይከፈታል፡፡
  7. የጨረታ መክፈቻዉ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለዉ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል ፡፡
  8. በጨረታ መክፈቻ ሰዓት አቅራቢዎች ወይም ወኪሎች ባይገኙም በጨረታ አከፋፈት ስርዓቱ ተገዥ ይሆናሉ ፡፡ አሸናፊዉ ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለፀበት ከ7/ሰባት/ቀን በኋላ ባሉት 8 ቀናት ዉስጥ ዉል መያዝ አለባቸዉ ፡
  9. ኢተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  10. ኢተርፕራይዙ 20በመቶ የመቀነስ ወይም  የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡
  11. በለጠ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 09 -11 -59 -13 -56 ወይም 09 -13- 42 -26 -44 ይደዉሉ፡፡ አድራሻ በአዊ አስ/ዞን እንጅባራ ከተማ እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ሱታና ንግድና የማማከር ስራዎች ኢተርፕራይዝ ነዉ፡፡

ሱታና ንግድና የማማከር ስራዎች ኢተርፕራይዝ

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here