ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

0
85

ባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ማዕከል በስሩ ያሉትን የካፌና ሬስቶራንት ክፍሎች በዘርፉ ልምድ ያላቸዉን ድርጅቶች በመለየት በጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. ለጨረታ የቀረቡ ክፍሎች ብዛትና አገልግሎት በጨረታ ሰነዱ (ስፔፊኬሽን) የሚገኝ ይሆናል፡፡
  2. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ክፍል የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 10,000(አስር
    ሽህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡ ተጨማሪ
    ክፍል ለመከራየት ፍላጎት ያለው ተጫራች ለተጨማሪ ክፍሉ ሌላ ማስያዣ ማስያዝ አለበት፡፡
  3. የጨረታ ሰነዱ ባህርዳር ከተማ ሆምላንድ ሆቴል አካባቢ በሚገኘው የአብክመ
    ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ግዥ፣ፋይ /ንብ /አስ/ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 11 ላይ የማይመለስ ብር 100 በመክፈል በስራ ሰዓት መግዛት ይቻላል፡፡
  4. የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ በአሀዝና በፊደል መገለፅ አለበት፡፡ ሆኖም በፊደልና በአሀዝ የተሞላው ልዩነት ካለው በፊደል የቀረበው መወዳደሪያ ዋጋ ብቻ ለወድድር ይቀርባል፡፡
  5. ተጫራቾች የፋይናንሽያል መወዳደሪያ የዋጋ ማቅረቢያና የዋስትና ማረጋገጫ ሲፒኦ በፓስታ በማሽግ በአብክመ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት፣ ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይችላሉ ፡፡
  6. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የጨረታ ዋጋ በሌሎች ተጫራቾች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ማቅረብ አይቻልም፡፡
  7. ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀና የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ሳጥኑ ታሽጎ በዚያው ቀን ከጥዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  8. ማዕከሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  9. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ማግኘት ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 222 22 70/058 226 21 77 ደውለው ማግኘት ይችላሉ፡፡

ባህር ዳር አለም አቀፍ ስታዲየም ማእከል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here