ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
72

የቢቡኝ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ቤት የግዥናን/አስ/ቡድን ለቢቡኝ ወረዳ እንስሳት ዓሳ ሀብት ፅ/ቤት የእንስሳት መድሐኒት በ2ዐ17 በጀት ዓመት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ለመጫረት የሚፈልግ ሁሉ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅበታል፡

  1. በአዲሱ አዋጅ መሠረት የታደሰ ንግድ ስራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/ቲን/ ያላቸው
  3. የግዥ መጠኑ ብር 200,000/ሁለት መቶ ሺ ብር/እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ቫት ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋገጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃ ኦርጅናልና ፎቶኮፒ ለየብቻዉ በማሸግና በእያንዳንዱ ፖስታ ላይ የግዥ ፈፃሚው እና የተጫራቹን ሙሉ ስምና አድራሻ ፊርማና ማህተም በማስቀመጥ ከጨራታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡
  5. አሸናፊ ተጫራች ማሸነፉ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት በ5 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ የጨረታ አሸናፊዉ የዉል ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋን 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ/ሲ.ፒ.ኦ/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና/በጥሬ ገንዘብ/ በመሂ1 ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  6. የመድሀኒቱን ዝርዝሩን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን 200/ሁለት መቶ ብር/ የማይመለስ ብር በመክፈል ከፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 12 ማግኘት ይችላሉ ።
  8. ተጫራቾች የጨራታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድቦንድ/ ለሚወዳደሩበት የመድሀኒት አቅርቦት ብር ጠቅላላ ዋጋ 10,000/ አስር ሽ ብር/ ብር በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ.ኦ/በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /ጥሬ ገንዘብ በመሂ1 ማስያዝ አለባቸው
  9. ተጫራቾች የጫራታ ሃሳባቸዉን ዋናውንና ቅጁን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በቢ/ወ/ገንዘብ/ጽ/ቤት በግዥ ን/አ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በተዘጋጀው የጫራታ ማስገቢያ ሳጥን ዘወትር በስራ ስዓት ከሚያዚያ 13/2017 እስከ ሚያዚያ 27/2017 ዓ/ም 11፡30 ሠዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በግዥ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በ16 ተኛዉ ቀን በ28/2017 ዓ.ም 3፡00 ሠዓት ይታሸጋል በዚሁ ቀን 3፡30 ይከፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨራታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን መ/ቤቱ 20 በመቶ የመጨመር የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  12. በነጠላም ሆነ በጠቅላላ ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለ ከፊት ለፈቱ መፈረም አለበት ።
  13. መ/ቤቱ ጨረታዉ የሚከፈትበት ቀን በአል ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቀን ይከፈታል።
  14. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈለጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 01 ድረስ በአካል በመገኘት /በስልክ ቁጥር 05825400474/49 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የቢቡኝ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here