የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች ባለው ክፍት የስራ መደብ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን ከሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎች መካከል በጊዜያዊ የረዥም ጊዜ (በኮንትራት) ቅጥር አወዳድሮ በመቅጠር ማሰራት ይፈልጋል፡፡
| ተ.ቁ | የሥራ መደቡ መጠሪያ | ደረጃ | የመ/መ/ቁ | ደመወዝ | ብዛት | ዳይሬክቶሬት/ዝግጅት | የሥራ ቦታ | ተፈላጊ የትምህርት ዝግጅት | ተፈላጊ የስራ ልምድ |
| 1. | የኦሮሚኛ ቋንቋ ሪፖርተር 1 | VIII | አሚ-732
አሚ-733
|
በኮርፖሬሽኑ የደመወዝ ስኬል መሠረት | 02 | ኦሮሚኛ ዝግጅት | ባ/ዳር | በብሮድካስት ጋዜጠኝነት፣ በጋዜጠኝነትና ተግባቦት፣ በተግባቦት (ኮምኒኬሽን) በስነ ጽሁፍ፣በቋንቋ፣ ፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት እና በተዛማጅ የትምህርት መስክ፡፡ | · የመጀመሪያ ዲግሪ 0 ዓመት የስራ ልምድ ከአማርኛ ቋንቋ በተጨማሪ የኦሮሚኛ ቋንቋ መስማት፣መናገር፣ ማንበብና መጻፍ የሚችሉ፡፡ |
ማሳሰቢያ፡–
- የምዝገባ ቀን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ይሆናል፡፡
- አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አመልካቾች በእምነት ማጉደል በማጭበርበር ወይም በስርቆት ወንጀል ተከሰዉ ከሆነ ስልጣን ባለዉ አካል ተፈርዶባቸዉ የመቀጠር መብታቸዉን እንዲጠቀሙ ስልጣን ያለዉ ፍርድ ቤት የወሰነበትን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- አመልካቾች ለፈተና በሚቀርቡበት ጊዜ ኦርጅናሉን የትምህርት መረጃ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ከተጠቀሰዉ የትምህርት ዝግጅት ውጭ ለምዝገባ የሚቀርቡ ሌሎች ማስረጃዎች ተቀባይነት አይኖራቸዉም፡፡
- አመልካቾች መልካም ስነ-ምግባር ያለው/ላት፣ ከማንኛውም ደባል ሱስ የፀዳ/ች፣ጥሩ ስብዕና ያላቸው መሆን አለባቸው ፡፡
- ተወዳዳሪዎች በተመዘገቡበት የስራ መደብ ለምን ተቀጥረው መስራት እንደፈለጉ በጽሁፍ ገልፀው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- አመልካቾች የሙያ ብቃት በሚያስፈልጋቸው የት/ት ዝግጅት የብቃት ማረጋገጫ በማስታወቂያው በተጠየቀው የት/ት ደረጃ ልክ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የሙያ ብቃት ምዘና ያልተጀመረባቸው የትምህርት መስኮች ከሚመለከተው ተቋም የሙያ ብቃት አለመጀመሩን ማስረጃ ካቀረቡ መመዝገብ ይችላሉ፡፡
- የኮንትራት ቅጥሩ ለ6 ወር ሆኖ እንደ አስፈላጊነቱ በየ6 ወሩ ይታደሳል፡፡
- ፈተና የሚሰጥበት ቀንና ቦታ በሌላ ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡
- አመልካቾች የምትመዘገቡበት ሊንክ በዌብሳይታችን ameco.et ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
- ወይም በተከታዩ ሊንክ https://forms.gle/97LaYYnMuRmQCyJz8 በመጫን መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እናሳስባለን፣
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 226 5007 አሚኮ ባህር ዳር ይደዉሉ፡፡
የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን
ባሕር ዳር

