በአመልካች አፈ/ከሳሽ ኑሪያ ካርሲማ፣ ጣ/ገብ እነ ሀይባ ካርሲማ እና በተጠሪ አፈ/ተከሳሽ ሙሀመድ አለምር መካከል ስላለው የባ/ሚስት ክርክር ጉዳይ በሙሀመድ አላምር ስም በባ/ዳር ከተማ በምድረ ገነት ቀበሌ ተመዝግቦ የሚገኘው፣ በምስራቅ እሩቅያ ሰይድ፣ በምእራብ አለም ወርቅ ገነቱ፣ በሰሜን መንገድ እንዲሁም በደቡብ የሽየ መካከል ተዋስኖ የሚገኘው 250 ካ.ሜ ቤት፤ የመነሻ ዋጋው 5‚047‚700.95 (አምስት ሚሊዩን አርባ ሰባት ሽህ ሰባት መቶ ብር ከዘጠና አምስት ሳንቲም) ሆኖ ይሸጣል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች፤ የመነሻ ዋጋውን በመያዝ፤ ጨረታው በሚካሄድበት ቦታ በመገኘት መጫረት የምትችሉ ሲሆን፤ የጨረታው ቀንም ግንቦት 22/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡00 እስከ 6፡00 ይካሄዳል፤ የጨረታ ማስታወቂያው ከሚያዚያ 19/2018 ዓ.ም እስከ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ድረስ በጋዜጣ ወጥቶ ይቆያል፡፡ ስለዚህ መጫረት የምትፈልጉ ሁሉ ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰአት ቤቱ በሚገኙበት ምድረ ገነት ድረስ በመገኘት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ማሳሰቢያ፡- አሸናፊው የሆነው በእለቱ ¼ በባንክ ያሲዛል፡፡
የባሕር ዳር ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት

