በአፈ/ከሳሽ አማኑ ሞነን እና በአፈ/ተከሳሽ እነ አጋዥ ፈንታሁን መካከል ባለው የገንዘብ ክርክር ጉዳይ በከሳ ከተማ 01 ቀበሌ በአዋሳኝ በምሥራቅ መንገድ ፣ በምዕራብ ፈንታሁን በላይ፣ በሰሜን እና በደቡብ መንገድ ተዋስኖ የሚገኘው መኖሪያ ቤት አጋዥ ፈንታሁን ስም ተመዝግቦ የሚገኘውን በመነሻ ዋጋ በብር 5,021,324.15 (አምስት ሚሊዮን ሃያ አንድ ሺህ ሶስት መቶ ሃያ አራት ብር ከአስራ አምስት ሳንቲም) ይሸጣል፡፡ በመሆኑም ከሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም እስከ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ30 ተከታታይ ቀናት በጋዜጣ ወጥቶ ቆይቶ ጨረታው ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 5፡00 እንዲሸጥ ሲል ፍርድ ቤቱ አዝዟል፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች ወደ ጨረታው ስትመጡ የጨረታውን መነሻ ዋጋ ¼ ኛውን በሲፒኦ ይዛችሁ እንድትቀርቡ፡፡
የባንጃ ወረዳ ፍርድ ቤት

