የላይ አርማጭሆ ወረዳ ፅ/ቤት በትክል ድንጋይ ከተማ ውስጥ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ ባለ 32 ቴፒዲና ብረት ተሸጦ ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ይፈልጋል ፡፡ የአንድ ብረት መነሻ ዋጋ ብር 14,032.59 ( አስራ አራት ሺህ ሰላሳሁለት ብር ከሀምሳዘጠኝ ሳንቲም ) ሲሆን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል ፡፡ ስለሆነም መግዛት የሚፈልግ ማንኛውም አካል የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት መወዳደር እንደሚችሉ አስታውቋል
- ተጫራቾች ጨረታውን ከወጣበት እስከ 15ኛው ቀን ድረስ ሰነዱን በመግዛት በላይ አርማጭሆ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ቤት በመግዛት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ
- ጫረታው በወታ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰአት ታሽጎ በዛውኑ ቀን 4፡30 በግልፅ ይከፈታል፡፡
- ዝርዝር መረጃውን ከጨረታ ሰነዱ ጋር ከሚገኘው ማስታወቂያ ታገኛላችሁ
ማሳሰቢያ ፅ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
የላይ አርማጭሆ ወረዳ ፅ/ቤት

