በምዕ/ጉጃም ዞን የቡሬ ዙሪያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በቡሬ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ንብረት ክፍል የሚገኘውን የተለያዩ ቢቢኤም ማረሻ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ድርጅቶች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- ተጫራቾች የሞሉት ጠቅላላ ዋጋ 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ) ብር እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ለመሆናቸው የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸው፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከተ.ቁጥር ከ1-3 የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ዋናውን ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታ ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፍኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ላይ ያገኛሉ፤ ሆናም ግን ብረታ ብረቶቹን በአካል ማየት ከፈለጉ ቡ/ዙ/ወ/ ግብርና ጽ/ቤት ንብረት ክፍል ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ አምስት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲፒዩ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከግንቦት 17/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ድረስ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በአንድ ወጥ በሆነ በታሸገ ፖስታ ዋና እና ፎቶ ኮፒውን ቡ/ዙ/ወ/ገ/ ጽ/ቤት ግዥ/ን/አስ/ ቡድን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ሰኔ 1/2018 ዓ.ም ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ታሽጐ 4፡30 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ግን የጨረታ መክፈቻ ቀኑ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ስዓት ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን ስርዝ ድልዝ ሳይኖር በዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ መሠረት የአንዱን ነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ ድምር በመሙላት የድርጅቱን ህጋዊ ማህተም ፊርማና አድራሻ በማስቀመጥ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለመውሰድ ብር 200 (ሁለት መቶ) ብር በመክፈል ሰነዱን ቡሬ ዙሪያ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ግዥ/ን/አስ/ ቡድን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ያሸነፈበትን የውል ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒዩ ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ አለባቸው፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥ/ን/አስ/ ቡድን በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 774 0237 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ሌሎች በጨረታ ማስታወቂያው ያልተካተቱ ሃሳቦች በግዥ መመሪያችን ቁጥር 1/2003 እና በሌሎች በተሻሻሉ የግንባታ የግዥ መመሪያዎች የምንገዛ ይሆናል፡፡
የቡሬ ዙሪያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

